ይህ ምስል አውሮፓና አሜሪካ እንዳይመስልዎ፤ ኢትዮጵያ እንጂ

ዛሬ የበረዶ ክምር የወረራት አሾካ ቀበሌ፣ ምዕራብ አርሲ ዞን ኮፈሌ ወረዳ

ዛሬ በምዕራብ አርሲ ዞን ውስጥ፤ ኮፈሌ ወረዳ አሾካ ቀበሌ የተከሰተ በረዶ ነው

ኢዛ (እሁድ መጋቢት ፲፫ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 22, 2020)፦ እንዲህ ያለው የበረዶ ክምር ሲታይ የተለያዩ የአውሮፓና የአሜሪካ ጎዳናዎች ይታወሳሉ። በምስሉ ላይ እንደሚታየው የበረዶ ክምሩ መንገዶችን ዘግቷል። አካባቢውንም ሸፍኗል። ይህ ግን አውሮፓ ሳይኾን የኾነው በምዕራብ አርሲ ዞን ውስጥ፤ ኮፈሌ ወረዳ አሾካ ቀበሌ ዛሬ መጋቢት 13 ቀን 2012 ዓ.ም. ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኮረና ቫይረስ በምርጫ 2012 ጣልቃ ገብቷል

ምርጫው መካሔድ አለመካሔድ እየተመረመረ ነው

ምርጫው መደረግ አለበት፤ የለበትም የሚለው ሙቀት እየተለካ ነው

ኢዛ (ዓርብ መጋቢት ፲፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 20, 2020)፦ በመጪው ነኀሴ 23 ቀን 2012 ዓ.ም. ይካሔዳል ተብሎ ቀን የተቆረተለት ምርጫ፤ አሁን በተከሰተው የኮሮና ቫይረስ ምክንያት መካሔድ አለመካሔዱ በምርጫ ቦርድ የሚወሰን መኾኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መሸታ ቤቶች ይዘጋሉ

Best Western Plus Addis Ababa

ኢዛ (ዓርብ መጋቢት ፲፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 20, 2020)፦ ዛሬ ማምሻውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ መግለጫ እንደሚያመለክተው፤ ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተገናኘ አገልግሎት እንዳይሠጡ ገደብ ከተጣለባቸው መካከል የምሽት መዝናኛ ቤቶች ወይም መሸታ ቤቶች ናቸው። (ኢዛ)

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ 30 አገሮች በረራ አቆመ

Ethiopian Airlines

ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ መንገደኞች ለ14 ቀኖች በልዩ ማቆያ የመቆየት ግዴታ ተጣለባቸው

ኢዛ (ዓርብ መጋቢት ፲፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 20, 2020)፦ በኮሮና ቫይረስ ሥርጭት ምክንያት በረራዎቹን እንዲያቋርጥ ተደጋጋሚ ውትወታ ሲደረግበት የነበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ፤ ወደ 30 አገሮች የሚያደርገውን በረራ አቋረጠ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኢትዮጵያ ስድስተኛው የቫይረሱ ተጠቂ ተገኘ

Coronavirus illustration

በጥቆማ በተደረገ ምርመራ በቫይረሱ የተያዘችው እንግሊዛዊት ነች

ኢዛ (ማክሰኞ መጋቢት ፰ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 17, 2020)፦ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ባወጣው መግለጫ አዲስ አበባ ውስጥ ኮሮና ቫይረስ ያለበት ሰው ተገኝቷል። ቫይረሱ የተገኘባት ስድስተኛዋ ሰው የ59 ዓመት ዕድሜ ያላት እንግሊዛዊት ዲፕሎማት ነች።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ራሳቸውን አግለው የቆዩት ዶክተር ቶላ ከቫይረሱ ነፃ መኾናቸው ታወቀ

ዶክተር ቶላ በሪሶ

ዶክተሩ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ኮሮና ቫይረስ ከተገኘበት ጃፓናዊ ጋር ንክኪ ነበራቸው

ኢዛ (ማክሰኞ መጋቢት ፯ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 17, 2020)፦ በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የኮሮና ቫይረስ ከተገኘበት ጃፓናዊ ጋር ንክኪ ነበራቸው ተብለው፤ በለይቶ ማቆያ ለብቻቸው ተቀምጠው የነበሩት የኦሮሚያ የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ቶላ በሪሶ፤ ከቫይረሱ ነፃ መኾናቸው ታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኮሮና ምክንያት ብሔራዊ ሙዚየም ከነገ ጀምሮ ለ15 ቀናት እንደሚዘጋ ተገለጸ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የነገውን ስብሰባ ሰረዘ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነገ ያካሒድ የነበረውን ስብሰባ ሰረዘ

ኢዛ (ሰኞ መጋቢት ፯ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 16, 2020)፦ ብሔራዊ ሙዚየም ለቀጣዮቹ አሥራ አምስት ቀናት ዝግ እንደሚኾን የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን አስታወቀ። የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም በነገው ዕለት ሊያካሒደው የነበረውን መደበኛ ስብሰባ ሰርዟል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኮሮና ቫይረስን በተመለከተ ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መመሪያ ተላለፈ

Prof. Hirut Woldemariam

ለ45 ዩኒቨርሲቲዎች መመሪያው ተላልፏል

ኢዛ (ሰኞ መጋቢት ፯ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 16, 2020)፦ ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትሯ ለሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት ሁሉም የመንግሥትና የግል ከፍተኛ ተቋማት ሊተግብሯቸው ይገባል ያሉትን መመሪያ አስተላለፉ። ይህ መመሪያ እንዲደርሳቸው የተደረጉት 45 ዩኒቨርሲቲዎች ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የኮሮና ቫይረስ ምርመር ላለማድረግ ያመለጠው ግለሰብ ከቫይረሱ ነፃ ኾነ

Wello

አምልጦ ደቡብ ወሎ ላይ ነበር የተያዘው

ኢዛ (ሰኞ መጋቢት ፯ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 16, 2020)፦ የኮሮና ቫይረስ ምልክቶች በማሳየቱ ተጨማሪ ምርመራ ሊደረግለት ሲል፤ አምልጦ ደቡብ ወሎ ላይ የተያዘው ግለሰብ የምርመራ ውጤት ከቫይረሱ ነፃ መኾኑን አመለከተ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ