ዛሬ ሦስት ተጨማሪ ሰዎች በኮሮና መያዛቸው ተረጋገጠ

3ዲ (3D) ኮሮና ቫይረስ በምስል (© istock.com/Dr_Microbe)

በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተያዙት ቁጥር 29 ደረሰ

ኢዛ (ረቡዕ መጋቢት ፳፫ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 1, 2020)፦ የጤና ሚኒስቴር ዛሬ መጋቢት 23 ቀን 2012 ዓ.ም. እንደገለጸው ከኾነ፣ የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ ከመረመራቸው 68 ሰዎች ውስጥ ሦስቱ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸውን አረጋግጧል። ይህም በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተያዙትን ቁጥር 29 አድርሶታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በዛሬው ዕለት ሁለት አዲስ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ግለሰቦች ተገኙ

የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት እና ጤና ሚኒስቴር

በኢትዮጵያ በኮሮና የተያዙት ቁጥር 21 ደረሰ

ኢዛ (እሁድ መጋቢት ፳ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 29, 2020)፦ የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ባደረገው ምርመራ ዛሬ መጋቢት 20 ቀን ሁለት ተጨማሪ ግለሰቦች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸውን ማረጋገጡን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። በድምሩ 21 ግለሰቦች በኢትዮጵያ ውስጥ መያዛቸው ታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ትምህርት ቤቶች ለተጨማሪ 15 ቀን እንዲዘጉ ተወሰነ

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት

መንግሥት በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ሌሎች ውሳኔዎችንም አሳልፏል

ኢዛ (ዓርብ መጋቢት ፲፰ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 27, 2020)፦ መንግሥት የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል ተጨማሪ ውሳኔዎችን ያስተላለፈ ሲሆን፣ ለ15 ቀናት እንዲዘጉ ተደርገው የነበሩ ትምህርት ቤቶች ለተጨማሪ 15 ቀናት ተዘግተው እንዲቆዩ ተወስኗል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት በተለያዩ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ውሳኔ ተሠጠ

PM Abiy Ahmed

ለግል ባንኮች 15 ቢሊዮን ብር እንዲፈቀድ ተወሰነ
በአበባ የወጪ ንግድ ላይ የተጣለው ዋጋ ጣራ ተነስቷል
ለወረርሽኙ መከላከያ ዕቃዎች ከቀረጥ ነፃ ይገባሉ

ኢዛ (ዓርብ መጋቢት ፲፰ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 27, 2020)፦ ከኮሮና ቫይረስ ጋር ተያይዞ በኢኮኖሚው ላይ ሊደርሱ የሚችሉ ተጽእኖዎችን ለመከላከልና ኢኮኖሚውን ደኅንነት ሊጠብቁ ይችላሉ የተባሉ ውሳኔዎች ተላልፈዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኮሮናን ለመከላከል የትግራይ ክልል አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጣ

Dr. Debretsion Gebremichael

የመዝናኛ ስፍራዎች፣ ጫት ቤቶች፣ የምሽት መዝናኛ ክለቦችና ሕዝብ የሚበዛባቸው ተቋማት እንዲዘጉ ተወስኗል

ኢዛ (ሐሙስ መጋቢት ፲፯ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 26, 2020)፦ የትግራይ ክልላዊ መንግሥት የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ያስችለኛል ያለውን የተለያዩ ውሳኔዎች ያሳረፈበትን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጥቷል። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን አስመልክተው ዛሬ መጋቢት 17 ቀን 2012 ዓ.ም. መግለጫውን የሠጡት የትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ናቸው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የመንግሥት ሠራተኞች ከነገ ጀምሮ ሥራ እንዳይገቡ ተወሰነ

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት

እያንዳንዱ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት የትኞቹ ሠራተኞቻቸው ከቤታቸው እንደሚሠሩ ይወስናሉ

ኢዛ (ማክሰኞ መጋቢት ፲፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 24, 2020)፦ የፌዴራል መንግሥት ሠራተኞች ከነገ መጋቢት 16 ቀን 2012 ዓ.ም. ጀምሮ ተጨማሪ ውሳኔ እስኪሠጥ ድረስ ሥራቸውን በቤታቸው ኾነው እንዲሠሩ ዛሬ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ባካሔደው 17ኛ አስቸኳይ ስብሰባ ወሰነ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሳሪስ አካባቢ በባቡር አንድ ሰው ገጭቶ ቆሟል

Addis Ababas tram

የገተጨው ግለሰብ በሕይወት መኖር አለመኖሩ አልታወቀም

ኢዛ (ሰኞ መጋቢት ፲፬ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 23, 2020)፦ ሳሪስ አደይ አበባ አካባቢ የከተማ ውስጥ ባቡር አንድ ሰው ላይ ግጭቶ ማድረሱ ተጠቆመ። የተገጨው ግለሰብ በሕይወት መኖር አለመኖሩ አልታወቀም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መንግሥት ለኮሮና ቫይረስ አምስት ቢሊዮን ብር መደበ

PM Abiy Ahmed

ከጎረቤት አገሮች ወደ ኢትዮጵያ በየብስ መግባት ተከለከለ

ኢዛ (ሰኞ መጋቢት ፲፬ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 23, 2020)፦ የኮሮና ቫይረስን (ኮቪድ-19) ሥርጭትን ለመቀነስና ለመከላከል መንግሥት 5 ሚሊዮን ብር መመደቡን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ አስታወቁ። ከጎረቤት አገሮች ወደ ኢትዮጵያ በየብስ የሚገቡ ማናቸውንም እንቅስቃሴዎች መታገዱንም አስታውቀዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ