ጄኔራሉ ብልጽግና ፓርቲን ተቀላቀሉ

B.Gen. Kemal Gelchu

ከኦነግና ከኦፌኮ ጋር ተፋትተዋል

ኢዛ (ማክሰኞ ነኀሴ ፳፮ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. September 1, 2020)፦ የቀድሞው የጦር መኮንንና የኦሮሞ ብሔራዊ ፓርቲ መሥራችና ሊቀመንበር ብርጋዲየር ጄኔራል ከማል ገልቹ ፓርቲያቸውን አክስመው የብልጽግና ፓርቲን ተቀላቀሉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ፖሊስ በአቶ ልደቱ ላይ ክስ ለመመሥረት የጠየቀው ተጨማሪ ቀን በፍርድ ቤቱ ውድቅ ኾነ

Lidetu Ayalew (Photo: Addis Fortune)

አቶ ልደቱ የዋስትና ጥያቄያቸውን በሌላ መዝገብ ማቅረብ ይችላሉ ተባለ

ኢዛ (ሰኞ ነኀሴ ፳፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. August 31, 2020)፦ በአቶ ልደቱ አያሌው ላይ ክስ እስኪመሠረት ተጨማሪ የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው የጠየቀው መርማሪ ፖሊስ፤ ጥያቄውን ፍርድ ቤቱ ውድቅ በማድረግ፤ አቶ ልደቱ በሌላ መዝገብ የዋስትና ጥያቄያቸውን እንዲያቀርቡ ትእዛዝ ተሰጠ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢዜማ በአዲስ አበባ መሬት ወረራና የኮንዶሚኒየም እደላ ዙሪያ አጀብ ያሰኘውን መረጃ ይፋ አደረገ

Prof. Berhanu Nega and Takele Uma

213,000 ካሬ ሜትር መሬት በሕገወጥ መንገድ ታድሏል
95 ሺሕ ኮንዶሚኒየም ቤቶች ላልቆጠቡ ሰዎች ተሰጥቷል
የዚህ ወንጀል ተባባሪዎች ለፍርድ ይቅረቡ ብሏል

ኢዛ (ሰኞ ነኀሴ ፳፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. August 31, 2020)፦ ኢዜማ በአዲስ አበባ ከ213,000 ካሬ ሜትር በላይ መሬት በሕገወጥ መንገድ መታደሉንና 95 ሺሕ የጋራ መኖሪያ ቤቶች በሕገወጥ መንገድ ለማይመለከታቸውና ለጋራ መኖሪያ ቤቶቹ ላልቆጠቡ ሰዎች መተላለፉን የሚያመለክተውን በጥናት ላይ የተደገፈ ሪፖርቱን ዛሬ ሰኞ ነኀሴ 25 ቀን 2012 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል። ጥናቱ የተጠናው በአዲስ አበባ ውስጥ ከሚገኙት አሥር ክፍለ ከተሞች ውስጥ በአምስቱ ክፍለ ከተሞች በተመረጡ 25 ቦታዎች ላይ ብቻ ነው። በዚህ ወንጀል እጃቸው ያለበት ባለሥልጣናት ለፍርድ ይቅረቡ ብሏል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሲኖዶሱ የአርቲስት ሐጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ የተፈጸመው ጥቃት ኦርቶዶክሳውያን ላይ ያነጣጠር ነው ሲል መግለጫ አወጣ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሲኖዶስ መግለጫውን በሰጠበት ወቅት

የፖለቲካ ፓርቲዎች ርዕዮተ ዓለማዊ ጥቃት በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ እያደረሱባት እንደኾነ ተገለጸ

ኢዛ (ረቡዕ ነኀሴ ፳ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. August 26, 2020)፦ የአርቲስት ሐጫሉ ሁንዴሳ ግድያን ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች የተፈጸመው ጥቃት ዋናው ዒላማ ኦርቶዶክሳውያን ምእመናን እንደነበሩ በመግለጽ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠንከር ያለ መግለጫ አውጥታለች። በፖለቲካ ፓርቲዎች ርዕዮተ ዓለማዊ ጥቃት እየደረሰባት እንዳለ ያስታወቀችው ቤተ ክርስቲያኒቱ፤ ከ67 በላይ ምእመናን በግፍ እና በአሠቃቂ ኹኔታ መገደላቸውን ከዐቢይ ኮሚቴው የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት መረዳትዋን አስታውቃለች።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር የህዳሴ ግድብን በመጎብኘት የመጀመሪያዊ መሪ ሊኾኑ ነው

PM Abiy Ahmed (L) and PM Abdalla Hamdok (R)

ጉብኝቱ ሱዳን ከኢትዮጵያ ወገን ስለመቆምዋ የሚያሳይ ተደርጎ ተወስዷል

ኢዛ (ረቡዕ ነኀሴ ፳ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. August 26, 2020)፦ የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሐምዶክ የታላቁን ህዳሴ ግድብ ለመጎብኘት የመጀመሪያው የተፋሰሱ አገር መሪ ሊኾኑ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በአንድ ቀን ምርመራ 1,778 የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች ተገኙ

Total coronavirus cases in Ethiopia, August 20, 2020

በቫይረሱ ተጠቅተው የሞቱት 620 ደርሰዋል

ኢዛ (ሐሙስ ነኀሴ ፲፬ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. August 20, 2020)፦ በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር አሳሳቢ በሚባል ደረጃ እየጨመረ በመምጣት፤ በአንድ ቀን 1,778 ሰዎች በቫይረሱ መጠቃታቸውን የሚያመለክት ሪፖርት ዛሬ ተደረገ። ከዚህ ቀደም ከፍተኛውና በአንድ ቀን ውስጥ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች የተመዘገበው ባለፈው ቅዳሜ ሲሆን፤ ቁጥሩም 1,652 ነበር። በአምስት ቀን ውስጥ በዛሬው ዕለት ያ አኀዝ በ126 ጭማሪ አሳይቷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በእነአቶ ጃዋር የክስ መዝገብ ምስክሮች መሰማት ጀመሩ

Jawar Mohammed

አቶ ጃዋር በግል እንዲታከሙ ትእዛዝ ተሰጥቷል

ኢዛ (ሐሙስ ነኀሴ ፲፬ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. August 20, 2020)፦ በእነአቶ ጃዋር መሐመድ መዝገብ ተቋርጦ የነበረው የዓቃቤ ሕግ ምስክሮችን የመስማት ሒደት ዛሬ ሐሙስ ነኀሴ 14 ቀን 2012 ዓ.ም. ተጀመረ። አቶ ጃዋር በማላውቀው ሐኪም መነካት አልፈልግም አለ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በሻሸመኔ በጸጥታ ኃይሎች ላይ ቦምብ የወረወረ የኦነግ ሸኔ አባል እርምጃ ተወሰደበት

የቦምብ ጥቃት በሻሸመኔ

አንድ የጸጥታ ኃይል ጉዳት ደርሶበት የሕክምና ክትትል እየተደረገለት ነው

ኢዛ (ሐሙስ ነኀሴ ፲፬ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. August 20, 2020)፦ ዛሬ ሐሙስ ነኀሴ 14 ቀን 2012 ዓ.ም. ጠዋት በሻሸመኔ ከተማ ቅኝት በሚያደርጉ የጸጥታ ኃይሎች ላይ ቦምብ ወረወረ በተባለ አንድ የኦነግ ሸኔ አባል ላይ እርምጃ መወሰዱን ፖሊስ አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወ/ሮ አዳነች አቤቤ የኢ/ር ታከለ ኡማን ሥልጣን ተረከቡ

Adanech Abebe and Eng. Takele Uma

አዲስ አበባ ከተማ አዲስ አበቤ ከንቲባ አሁንም አላገኘችም

ኢዛ (ማክሰኞ ነኀሴ ፲፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. August 18, 2020)፦ ከአዲስ አበባ ከተማ ምክልት ከንቲባነታቸው ተነስተው የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስትር ኾነው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተሾሙት ኢንጂንየር ታከለ ኡማ ምትክ የከተማዋ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ የከተማ ምክትል ከንቲባ ኾነው ተሾሙ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አቶ ለማ መገርሳ ከመከላከያ ሚኒስትርነታቸው ተነሱ

Ato Lemma Megersa

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ሹምሽር አካሔዱ

ኢዛ (ማክሰኞ ነኀሴ ፲፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. August 18, 2020)፦ በዛሬው ዕለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ለአሥር ሰዎች ሹመት መስጠታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ። ኢንጂንየር ታከለ ኡማ ከአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባነት ተነስተው የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስትር ኾነው ተሹመዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ