ጄኔራሉ ብልጽግና ፓርቲን ተቀላቀሉ
ከኦነግና ከኦፌኮ ጋር ተፋትተዋል
ኢዛ (ማክሰኞ ነኀሴ ፳፮ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. September 1, 2020)፦ የቀድሞው የጦር መኮንንና የኦሮሞ ብሔራዊ ፓርቲ መሥራችና ሊቀመንበር ብርጋዲየር ጄኔራል ከማል ገልቹ ፓርቲያቸውን አክስመው የብልጽግና ፓርቲን ተቀላቀሉ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ማክሰኞ ነኀሴ ፳፮ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. September 1, 2020)፦ የቀድሞው የጦር መኮንንና የኦሮሞ ብሔራዊ ፓርቲ መሥራችና ሊቀመንበር ብርጋዲየር ጄኔራል ከማል ገልቹ ፓርቲያቸውን አክስመው የብልጽግና ፓርቲን ተቀላቀሉ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ሰኞ ነኀሴ ፳፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. August 31, 2020)፦ በአቶ ልደቱ አያሌው ላይ ክስ እስኪመሠረት ተጨማሪ የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው የጠየቀው መርማሪ ፖሊስ፤ ጥያቄውን ፍርድ ቤቱ ውድቅ በማድረግ፤ አቶ ልደቱ በሌላ መዝገብ የዋስትና ጥያቄያቸውን እንዲያቀርቡ ትእዛዝ ተሰጠ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ሰኞ ነኀሴ ፳፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. August 31, 2020)፦ ኢዜማ በአዲስ አበባ ከ213,000 ካሬ ሜትር በላይ መሬት በሕገወጥ መንገድ መታደሉንና 95 ሺሕ የጋራ መኖሪያ ቤቶች በሕገወጥ መንገድ ለማይመለከታቸውና ለጋራ መኖሪያ ቤቶቹ ላልቆጠቡ ሰዎች መተላለፉን የሚያመለክተውን በጥናት ላይ የተደገፈ ሪፖርቱን ዛሬ ሰኞ ነኀሴ 25 ቀን 2012 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል። ጥናቱ የተጠናው በአዲስ አበባ ውስጥ ከሚገኙት አሥር ክፍለ ከተሞች ውስጥ በአምስቱ ክፍለ ከተሞች በተመረጡ 25 ቦታዎች ላይ ብቻ ነው። በዚህ ወንጀል እጃቸው ያለበት ባለሥልጣናት ለፍርድ ይቅረቡ ብሏል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ረቡዕ ነኀሴ ፳ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. August 26, 2020)፦ የአርቲስት ሐጫሉ ሁንዴሳ ግድያን ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች የተፈጸመው ጥቃት ዋናው ዒላማ ኦርቶዶክሳውያን ምእመናን እንደነበሩ በመግለጽ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠንከር ያለ መግለጫ አውጥታለች። በፖለቲካ ፓርቲዎች ርዕዮተ ዓለማዊ ጥቃት እየደረሰባት እንዳለ ያስታወቀችው ቤተ ክርስቲያኒቱ፤ ከ67 በላይ ምእመናን በግፍ እና በአሠቃቂ ኹኔታ መገደላቸውን ከዐቢይ ኮሚቴው የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት መረዳትዋን አስታውቃለች።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ረቡዕ ነኀሴ ፳ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. August 26, 2020)፦ የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሐምዶክ የታላቁን ህዳሴ ግድብ ለመጎብኘት የመጀመሪያው የተፋሰሱ አገር መሪ ሊኾኑ ነው።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ሐሙስ ነኀሴ ፲፬ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. August 20, 2020)፦ በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር አሳሳቢ በሚባል ደረጃ እየጨመረ በመምጣት፤ በአንድ ቀን 1,778 ሰዎች በቫይረሱ መጠቃታቸውን የሚያመለክት ሪፖርት ዛሬ ተደረገ። ከዚህ ቀደም ከፍተኛውና በአንድ ቀን ውስጥ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች የተመዘገበው ባለፈው ቅዳሜ ሲሆን፤ ቁጥሩም 1,652 ነበር። በአምስት ቀን ውስጥ በዛሬው ዕለት ያ አኀዝ በ126 ጭማሪ አሳይቷል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ሐሙስ ነኀሴ ፲፬ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. August 20, 2020)፦ በእነአቶ ጃዋር መሐመድ መዝገብ ተቋርጦ የነበረው የዓቃቤ ሕግ ምስክሮችን የመስማት ሒደት ዛሬ ሐሙስ ነኀሴ 14 ቀን 2012 ዓ.ም. ተጀመረ። አቶ ጃዋር በማላውቀው ሐኪም መነካት አልፈልግም አለ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ሐሙስ ነኀሴ ፲፬ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. August 20, 2020)፦ ዛሬ ሐሙስ ነኀሴ 14 ቀን 2012 ዓ.ም. ጠዋት በሻሸመኔ ከተማ ቅኝት በሚያደርጉ የጸጥታ ኃይሎች ላይ ቦምብ ወረወረ በተባለ አንድ የኦነግ ሸኔ አባል ላይ እርምጃ መወሰዱን ፖሊስ አስታወቀ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ማክሰኞ ነኀሴ ፲፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. August 18, 2020)፦ ከአዲስ አበባ ከተማ ምክልት ከንቲባነታቸው ተነስተው የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስትር ኾነው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተሾሙት ኢንጂንየር ታከለ ኡማ ምትክ የከተማዋ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ የከተማ ምክትል ከንቲባ ኾነው ተሾሙ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ማክሰኞ ነኀሴ ፲፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. August 18, 2020)፦ በዛሬው ዕለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ለአሥር ሰዎች ሹመት መስጠታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ። ኢንጂንየር ታከለ ኡማ ከአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባነት ተነስተው የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስትር ኾነው ተሹመዋል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...