በቡራዩ ጥቃት ተጠርጣሪዎች እየተያዙ ነው
እስካሁን 17 ተጠርጣሪዎች በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለዋል
ኢዛ (ቅዳሜ የካቲት ፲፮ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 22, 2020)፦ ባለፈው ዓርብ የካቲት 13 ቀን 2012 ዓ.ም. በቡራዩ ከተማ የደረሰውን ጥቃት በማቀነባበርና በመተግበር ተሳታፊ በመኾን የተጠረጠሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር ስለመዋላቸው እየተገለጸ ነው።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ቅዳሜ የካቲት ፲፮ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 22, 2020)፦ ባለፈው ዓርብ የካቲት 13 ቀን 2012 ዓ.ም. በቡራዩ ከተማ የደረሰውን ጥቃት በማቀነባበርና በመተግበር ተሳታፊ በመኾን የተጠረጠሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር ስለመዋላቸው እየተገለጸ ነው።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ዓርብ የካቲት ፲፫ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 21, 2020)፦ ዛሬ ምሳ ሰዓት ላይ የቡራዩ የጸጥታ ዘርፍ ኃላፊ በታጠቁ ኃይሎች ተተኮሰባቸው ሲገደሉ፤ አብረዋቸው የነበሩ የፖሊስ አዛዥም በጥይት መመታታቸው ተገለጸ። ይህ አሳዛኝ ድርጊት የተፈጸመው የቡራዩ ከተማ የጸጥታ ኃላፊ አቶ ሰለሞን ታደሰና ሌሎች ሰዎች ምሳ በመብላት ላይ እያሉ ነው።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ሐሙስ የካቲት ፲፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 20, 2020)፦ ኢሕአዴግ ሥልጣን በያዘ በሁለተኛ ዓመቱ በ1985 ዓ.ም. ተሰርቆ የነበረውና ከ400 ዓመት በላይ ዕድሜ ያለው የኢትዮጵያ ዘውድ በዛሬው ዕለተ ለኢትዮጵያ ተመለሰ። ዘውዱ የተዘረፈው መቀሌ አካባቢ ከሚገኘው የሥላሴ ጨለቆት ቤተ ክርስቲያን እንደኾነ ታውቋል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ሐሙስ የካቲት ፲፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 20, 2020)፦ በ1929 ዓ.ም. ልክ በዛሬዋ ዕለት (የካቲት 12 ቀን)፤ የፋሺስት ጣሊያን የጦር መሪ ጄኔራል ሩዶልፍ ግራዚያኒ በቤተመንግሥት የአዲስ አበባን ሕዝብ ጠርቶ ንግግር ሲያደርግ፤ ኢትዮጵያ በመወረሯ ሲቃጠሉ የነበሩ ሁለት ጀግና ወጣቶች የእጅ ቦንብ በመወርወር የመግደል ሙከራ ያደረጉባት ቀን ናት። የአገራቸው ጉዳይ ያንገበገባቸው ወጣቶቹ፤ አብርሃም ደቦጭና ሞገስ አስገዶም ናቸው። ይኽ ከኾነ ዛሬ 83ኛ ዓመቱ ነው። ዕለቱም “የሰማእታት ቀን” እየተባለ ይከበራ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ረቡዕ የካቲት ፲፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 19, 2020)፦ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሲኖዶስ በቅርቡ በአዲስ አበባ ከተማ 22 ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የተፈጸመውን ድርጊት ያወገዘ፣ ከቤተክርስቲያኑ ሕግና ደንብ ውጭ የኦሮሚያ ቤተ ክህነት እናቋቁማለን በማለት የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦችን ማገዱን፣ እንዲሁም በሌሎች ወቅታዊ ጉዳዮች ውሳኔ የደረሰበትን መግለጫ አወጣ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ረቡዕ የካቲት ፲፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 19, 2020)፦ የሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ሕወሓት 45ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ዛሬ የካቲት 11 ቀን 2012 ዓ.ም. በመቀሌ ስታዲየም ተከብሯል። ዶ/ር ደብረጽዮን፤ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትን በእነርሱ ላይ ይካሔዳል ያሉትን ዘመቻ አስቁሙልን ወይም ትግራይ ራስዋን የቻለች አገር እንድትኾን ወስኑ አሉ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ረቡዕ የካቲት ፲፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 19, 2020)፦ የኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር በመኾን ሲያገለግሉ የቆዩት አቶ ሽመልስ አብዲሳ በዛሬው ዕለት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር በመኾን ተሹመው፤ ቃለ መሃላ ፈጸሙ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ረቡዕ የካቲት ፲፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 19, 2020)፦ በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ ከተሞች ለብልጽግና ፓርቲና ለዶክተር ዐቢይ አሕመድ ድጋፍ ለመሥጠት የሚካሔዱ ሰላማዊ ሰልፎች ቀጥለዋል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ማክሰኞ የካቲት ፲ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 18, 2020)፦ የትግራይ ክልል የብልጽግና ፓርቲ አባላትና አመራሮች ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ጋር መምከራቸው ተገለጸ። እስካሁን በትግራይ ክልል የብልጽግና ቅርንጫፍ ስለመኖሩ ባይገለጽም፤ ዛሬ ይፋዊ መረጃ በትግራይ ክልል የብልጽግና ፓርቲን የሚወክል አካል መኖሩ ታውቋል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...
ኢዛ (ማክሰኞ የካቲት ፲ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 18, 2020)፦ “ፒክ ፒክ” የተሰኘውና ዘመናዊ የታክሲ አገልግሎት ለመሥጠት የተቋቋመው ድርጅት ከአንድ ዓመት በላይ አገልግሎት ሲሠጥ የቆየ ቢኾንም፤ የ“ፒክ ፒክ” ታክሲዎች እንዳይንቀሳቀሱ በፍርድ ቤት ታገቱ። የታክሲ ሹፌሮቹም ከሥራ ታገዱ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...