በኮሮና ቫይረስ የተያዙት ሰዎች ቁጥር 11 መድረሱን ስዊድን አስታወቀች

Coronavirus in Sweden

በዛሬው ዕለት አራት፣ ትናንት ደግሞ አምስት ተጨማሪ ሰዎች በኮሮና ቫይረስ ተይዘዋል ተባለ

ኢዛ (ዓርብ የካቲት ፳ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 28, 2020)፦ በዛሬው ዕለት አራት ሰዎች በሦስት የተለያዩ ከተሞች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው መረጋገጡን የስዊድን መገናኛ ብዙኀን ዘገቡ። በትናንትናው ዕለት ደግሞ አምስት ሰዎች፣ ከትናንት በስቲያ አንድ፣ ከሳምንታት በፊት አንድ ሰው በቫይረሱ የተያዙ መኖራቸው ታውቋል። እስካሁን በስዊድን በቫይረሱ የተያዙት ቁጥር አስራ አንድ ደርሷል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያውያን በህዳሴ ግድብና በዓባይ ወንዝ አጠቃቀም ላይ የአሜሪካ መንግሥትን አድሎአዊ ጣልቃ ገብነት በዋሽንግተን ተቃወሙ

“ድሃ ወገኖቻችን አንጀታቸውን ቋጥረው በሠሩት ግድብ አንደራደርም!”

“ዓባይ የእኛም ጭምር ነው” ኢትዮጵያውያን

ኢዛ (ሐሙስ የካቲት ፲፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 27, 2020)፦ በታላቁ ህዳሴ ግድብና በዓባይ ወንዝ አጠቃቀም ዙሪያ የአሜሪካ መንግሥት አድሎአዊ ጣልቃ ገብነት በመቃወም፤ ኢትዮጵያውያን በዋሽንግተን ዲሲ የሚካሔደው ሰልፍ ተጀምሯል። በዚህ ሰልፍ ላይ ኢትዮጵያውያን “ዓባይ የእኛም ጭምር ነው!” ሲሉ ተደምጠዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ልማት ባንክ የተበላሸ ብድሩን ከ40 ወደ 34 በመቶ ማውረዱን ገለጸ

Development Bank of Ethiopia

በአራት ዓመት ውስጥ የተበላሸ ብድሩን 10 በመቶ ለማድረስ አቅዷል

ኢዛ (ሐሙስ የካቲት ፲፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 27, 2020)፦ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የተበላሸ የብድር መጠኑን ከ40 በመቶ ወደ 34 በመቶ ያወረደ መኾኑን ዛሬ የባንኩ ባለሥልጣን በሠጡት መግለጫ አስታውቀዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አቶ ዮሐንስ ቧያለው አዲሱ ሹመት እንደማይቀበሉ አሳወቁ

አቶ ዮሐንስ ቧያለው ከአማራ ማስ ሚዲያ ጋር ባደረጉት ቆይታ

የመለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ ፕሬዝዳንት ኾነው በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተሾሙት ትናንት ነበር

ኢዛ (ረቡዕ የካቲት ፲፰ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 26, 2020)፦ በትናንትናው ዕለት በጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የመለስ ዜናዊ አመራር አካዳሚ ፕሬዝዳንት እንዲኾኑ የተሾሙት አቶ ዮሐንስ ቧያለው፤ ሹመቱን ለመቀበል እንደሚቸገሩ ዛሬ ገለጹ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢትዮጵያ ነገ በአሜሪካ ሊካሔድ በነበረው የህዳሴ ግድብ ውይይት ላይ አልገኝም አለች

The Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD)

ምክንያቷ ከባለድራሻ አካላት ጋር የምታደርገውን ውይይት ባለመጨረስዋ መኾኑን አስታውቃለች

ኢዛ (ረቡዕ የካቲት ፲፰ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 26, 2020)፦ በዋሽንግተን ዲሲ ነገ ሊጀመር በነበረው የታላቁ የህዳሴ ግድብ ላይ ኢትዮጵያ እንደማትገኝ ዛሬ አስታወቀች።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የ60 ተጠርጣሪዎች ክስ ተቋርጦ ምሕረት እንደተደረገላቸው ተገለጸ

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት

ስም ዝርዝራቸው ነገ ማክሰኞ ይገለጻል

ኢዛ (ሰኞ የካቲት ፲፮ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 24, 2020)፦ መንግሥት ጉዳያቸውን በሕግ ሲከታተሉ ነበሩ ያላቸውን 60 ተጠርጣሪዎች ምሕረት እንዳደረገላቸው አስታወቀ። ስም ዝርዝራቸው ነገ ማክሰኞ ይገለጻል ተብሏል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የቀድሞዎቹ ጠቅላይ ሚኒስትሮች የኢኮኖሚ አማካሪ አቶ ንዋይ ገብረአብ አረፉ

አቶ ንዋይ ገብረአብ

ለሃያ አምስት ዓመታት በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ከፍተኛ ሚና ነበራቸው

ኢዛ (ሰኞ የካቲት ፲፮ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 24, 2020)፦ የቀድሞዎቹን ጠቅላይ ሚኒስትሮች በኢኮኖሚ አማካሪነት ሲያገለግሉ የቆዩትና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክን በቦርድ ሊቀመንበርነት በመምራት የሚታወቁት አቶ ንዋይ ገብረአብ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በአምቦ ጥቃት የኦነግ ሸኔ እጅ እንዳለበት የፖሊስ ገለጸ

ኮሚሽነር አራርሳ መርደሳ

በቡራዩ ግድያም የኦነግ ሸኔ አባሎች መኾናቸው ተጠቁሟል

ኢዛ (እሁድ የካቲት ፲፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 23, 2020)፦ በአምቦ የተፈጸመውን የቦምብ ጥቃት በኦነግ ሸኔ የተፈጸመ ስለመኾኑ ተጠቆመ። ይህንን የገለጹት የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽነር ጥቃቱን ካደረሱት ተጥርጣሪዎች መካከል ይህንን የሚያረጋግጥ መረጃ በመገኘቱ ነው ብለዋል። በቡራዩ ግድያም የኦነግ ሸኔ አባሎች መኾናቸው ተጠቁሟል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በአምቦ የድጋፍ ሰልፍ ላይ ቦምብ መወርወሩ ተሰማ

በአምቦ ለብልጽግናና ለዶክተር ዐቢይ የተካሔደው የድጋፍ ሰልፍ በከፊል

ከ20 በላይ ሰዎች ተጎድተዋል

ኢዛ (እሁድ የካቲት ፲፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 23, 2020)፦ ዛሬ ጠዋት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድና ለብልጽግና ፓርቲ ያላቸውን ድጋፍ ለመግለጽ በአምቦ በተካሔደው ትዕይንተ ሕዝብ መሐል ቦምብ ተውርውሮ ጉዳት መድረሱ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ