የረቡዕ ግጥም ፴፬
ቀኑ ልማዱ ነው ይመሻል ይነጋል
መብራቱም እንደዛው ይሄዳል ይመጣል
ዝግጅት እናድርግ ሻማ ለመለኮስ
አይቀርም መጥፋቱ ካዲስ'አባ መለስ
ሙሉውን አስነብበኝ ...




ቀኑ ልማዱ ነው ይመሻል ይነጋል
መብራቱም እንደዛው ይሄዳል ይመጣል
ዝግጅት እናድርግ ሻማ ለመለኮስ
አይቀርም መጥፋቱ ካዲስ'አባ መለስ
ሙሉውን አስነብበኝ ...




በጭለማ መሃል ምንም በሌለበት
በዚህ በአሁን ዘመን የተገኘህ ወጣት
ዝምታህ ምንድነው ሰምተህ ነው ሳትሰማ
በየአደባባዩ እንዲህ ስትታማ
ማንም አይመጣልህ አንተ ራስህ መልስ
ከናት ካባቶችህ ምን አገኘህ በውርስ
ሙሉውን አስነብበኝ ...የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5





ደግ መሃል ገብቶ ”ር” ተወትፎ
ደርግ አደረገብን ይህ የፊደል መጥፎ
አሁን ደግሞ ይሄው ”ያ” ክፉ ሸፋፋ
ወኔ መሃል ገብቶ ሀገርን አጠፋ
እኛ ባንቸኩል ዘመኑም ባይከዳን
ቀስ መሃል ሆኖ ”ኃ” ነበር ሚሻለን
ሙሉውን አስነብበኝ ...




መጨበጫም የለው መቼም የኔ ጣጣ
በሀገሬም አልኖር ካገሬም አልወጣ
እዛ ስሆን እዚ ከዚ እዛ እያሰብኩኝ
ማደሪያ የሌለው ከንቱ አሞራ ሆንኩኝ
ሙሉውን አስነብበኝ ...




ፍራቻ ሠልጥኖ እጅግ ተቀናጣ
ገደቡን ዘለለ ከአናት በላይ ወጣ
ግፍ ስቃይ መከራ ይበቃናል ባልኩኝ
እንኳንስ ሌላውን እራሴ እኔን ፈራኝ ሙሉውን አስነብበኝ ...





ምንም ነገር ሳልይዝ ባዶዬን መጥቼ
እውቀት በመሰለኝ ክፋት ተሞልቼ
ግዜዬን ስጨርስ ከዝች ዓለም ስሄድ
ማምለጫዬን እንጃ ከሚጠብቀኝ ፍርድ ሙሉውን አስነብበኝ ...
የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5





ተጨነቅ ያለው ሰው አዕምሮው አይረፍ
ያሻው የወደደው ሞልቶ ቢትረፈረፍ
የነገውን ስቦ ያምናውን ጎትቶ
ሲፈጭ ነው የሚኖር ሳይጋግር አቡክቶ
ሙሉውን አስነብበኝ ...




አላህ ቢሻ ኖሮ ብዙ እንድንናገር
አፍን ሁለት አድርጎ በፈጠረ ነበር
ሆኖም በመውደዱ ብዙ እንዳናወራ
አፍን አንድ አደርጎ ሁለት ጆሮ ሠራ
ሙሉውን አስነብበኝ ...የአንባብያን ድምፅ: 5 / 5





ህይወት አስተምሮት ካልመለሰው በቀር
አድናለሁ ብለህ ይሄን ሰው በምክር
ያለህን አሟጠህ ጆሮው ብትገለብጥ
እመነኝ ጨርሶ አትችልም መለወጥ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...የአንባብያን ድምፅ: 3 / 5





ልክ እንደሥራህ አታጣምና
ደጋግ ጣቶች ቀና ልቦና
ይኑርህ ጎበዝ ደግነት ተማር
ምርጫ ከመጣም እሷው ላይ አጥቁር ሙሉውን አስነብበኝ ...