አዲሱ የልመና ሚኒስትር (ጭውውት)
አዲሱ የልመና ሚኒስትር
(ጭውውት)
ዳግማዊ ዳዊት

ከሚስጥር ኪሴና ከእናቱ መቀነት - በሚያገኘው ሽልንግ
ልጀ ሰይፈ ፋንታ - ልክ እንደ አገሬው ወግ
ጥሩ አርጎ አሳዳገው - ቀንዳሙን ዳሌ በግ።

ሙክቱን ሳናርደው - ወይም ሳንሸጠው
ደርግ የአገሬውን ሰው - በመትረየስ ሲያጭደው
ልጀ ሸፈተና - ኢህአሠ ውስጥ ገብቶ
ድፍን ዓመት ቆዬ - ውጊያው ተበራቶ።
በረሃ ቆይቶ - ጎንደርና ጎጃም - ትግራይም ገስግሶ
ልጀ ሰይፈ ፋንታ - ወልዲያ ተመልሶ
የጀግና አቀባበል - ላደርግ ወሰንኩና
መሸትሸት እንዳለ - ሙከቴን አርጀ
ጠዋት አነጋግ ላይ - ቆዳውን እንዲሸጥ - ሰጠሁት ለልጀ
ከቤታችን ማዶ - ያለውም ነጋዴ - ቆዳውን አየና
ከልጀ ወሰደው - ሰባት ብር ሰጠና።
ከወልዲያ ደሴ - ከደሴ ኮምቦልቻ - ከኮምቦልቻም ሸገር
ከሸገር ጅቡቲ - አርጎ በቀይ ባህር
ተሻግሮ ውጭ አገር - ቆዳው ተሸጠና
በአማሪካ ምድር - የአባ ፋንታ ቆዳ - እጅግ ከበረና
የሳልሞን ቸዝ ምስል - የአብርሃም ሊንከን
ላዩ ላይ ተስሎ - አለና ሽቅርቅር
መዳፍ - መዳፍ ያክል - ሆኖ ተቆራርጦ - ሆኖ በብዛት
ተብሎ ተከትቦበት - “ሕጋዊ ገንዘብ ነው - የአሜሪካ ሀብት”
ሚሊዮን መቶ ሽ …
ሃምሳ፤ መቶ ና ሽህ - ላዩ ላይ ተፅፎ
ካዝና ውስጥ ገባ - በጥብቅ ተቆልፎ።
ልጄም ከኢህአሠ - መስማማት አቅቶት
መንገዱን አቀና - ሊገናኝ ከተሃት
እዚያም ሳይሳካ ድርቡሽ አገር ገብቶ - ዓመት እንደቆዬ
አማሪካ ገባ - አለኝ እሱን ያዬ።
ዓመታት ነጎዱ - የእኔም ልጅ ተማረ - በሶላቶ መምር
የምጣኔ ሀብትን - የሚያስችል ምርምር
ከዚያም ባንክ ገብቶ - ሥራ ጀመረና
ለጥቂት ዓመታት - ያሳደገውን በግ - ቆዳ ቆጠረና
የምስር የድርቡሽ - የነጭ ምትሃት - ተሃትን ወንድ አርጎ
መንግሥት ሲገለብጥ - ሰይፈም ሰበብ አርጎ
ከዲ.ሲ. ተሳፍሮ - ኢትዮጵያ ገባና
የመለስ አገልጋይ - መሆን ወሰነና
“ኤክስፐርት” ተብሎ - ትልቁ ካቢኔ
ሲለምን ሰማሁት - ይኽው አየሁ ባይኔ።
የዝያን ዳሌ በጌን - የከበረ ቆዳ
ማስገኘት የሚያስችል - ለአገሪቱ በዕዳ
አልያም ለምፅዋት - ብልሃት ፍለጋ
ሊሠራ የእኔ ልጅ - አገር የሚጎዳ
ዛሬ መለስ ሾመው - ሚኒስትር ነህ አለው
የሸጠውን ቆዳ - ለማኝ አደረገው።
ዳግማዊ ዳዊት
This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.
መስከረም 2003 ዓ.ም.



