ለትግራይ ልዩ ኃይልና ሚሊሺያ የተሰጠው የ72 ሰዓት ጊዜ ገደብ አለቀ

PM Abiy Ahmed

የጊዜ ገደብ ስላለቀ ወደ መጨረሻው የሕግ ማስከበር ሥራ እንደሚገባ ዶ/ር ዐቢይ አስታወቁ

ኢዛ (ማክሰኞ ኅዳር ፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 17, 2020)፦ የትግራይ ልዩ ኃይልና ሚሊሽያ የስግብግቡ ጁንታ እኩይ ዓላማ ማስፈጸሚያ ከመኾን ይልቅ እጁን እንዲሰጥ የተሰጠው የሦስት ቀን የጊዜ ገደብ በመጠናቀቁ፤ ወደ መጨረሻው የሕግ ማስከበር ተግባር እንደሚገባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ገለጽ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በየአካባቢው ከፍተኛ መጠን ያላቸው የጦር መሣሪያዎች እየተያዙ ነው

ሕወሓት ሊጠቀምባቸው የነበሩና በአማራ ፖሊስ መያዛቸው ከተገለጹት መሣሪያዎች በከፊል

በአዲስ አበባ አንድ ሺህ ሽጉጦች ተይዘዋል
በሑመራ ከፍተኛ መጠን ያለው የጦር መሣሪያ ተይዟል፤ በሱር ኮንሽትራክሽን ካምፕ ውስጥ ጭምር

ኢዛ (ሰኞ ኅዳር ፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 16, 2020)፦ ባለፉት ጥቂት ቀናት በተደረጉ ፍተሻዎች ከአንድ ሺህ በላይ ሽጉጦችን ጨምሮ ሌሎች በርካታ የጦር መሣሪያዎችን መያዙን የፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ። በቃፍታ ሑመራ በሚገኘውና በሕወሓት ባለቤትነት በሚተዳደርው የሱር ኮንስትራክሽንም በርካታ የጦር መሣሪያዎች ተይዘዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በቤንሻንጉል ጉሙዝ ዘግናኝ ጥቃት መፈጸሙን ኮሚሽኑ አስታወቀ

ቤንሻንጉል ጉሙዝ

ጥቃቱ የተፈጸመው እየተጓዘ ባለ አውቶቡስ ላይ ነው
በጥቃቱ እስካሁን 34 ንጹኀን ዜጎች ተጎጂ ኾነዋል

ኢዛ (እሁድ ኅዳር ፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 15, 2020)፦ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል በመጓዝ ላይ ባለ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ላይ ዘግናኝ ነው ባለው ጥቃት ጉዳይ እንደደረሰ አመለከተ። እስካሁን በደረሰው መረጃ በዚህ ጥቃት 34 ሰዎች እንደተጎዱና ይህ ቁጥር እንደሚጨምር የሚጠበቅ መኾኑን፤ “ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጸጥታና ደኅንነት ለማጠናከር ፈጣንና የተቀናጀ እርምጃ አስፈላጊ ነው” በሚል ርዕስ ባወጣው መግለጫ አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በሕወሓት ባለቤትነት በሚመራው ሱር ኮንስትራክሽን 23 የረዥም ርቀት መገናኛ ራዲዮኖች፣ 92 የእጅ መገናኛዎች፣ 67 የስልክ መጥለፊያ መሣሪያዎች ተያዙ

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው (ግራ) እና በሦስት ቀናት ውስጥ በአዲስ አበባ ከተያዙት ሕገወጥ መሣሪያዎች በጥቂቱ

242 የሕወሓት ተላላኪዎች ተይዘው ምርመራ እየተጣራባቸው ነው
በሦስት ቀናት 744 የጦር መሣሪያዎችና 4628 ጥይቶች ተይዘዋል

ኢዛ (ሐሙስ ኅዳር ፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 12, 2020)፦ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በከተማዋ በሦስት ቀናት በተደረገ ፍተሻና ብርበራ 744 የጦር መሣሪያዎች፣ 4628 ጥይቶች፣ እንዲሁም የሕወሓት ጁንታ ቡድንን ተልዕኮ ተቀብለው ለማስፈጸም ሲንቀሳቀሱ የተገኙ 242 ተላላኪዎችን መያዙን አስታወቀ። ሕወሓት (ኤፈርት) በሚያስተዳድረው ሱር ኮንስትራክሽን ድርጅት ውስጥ ደግሞ ለሕገወጥ ተልዕኮ ማስፈጸሚያ ሊውል የነበረ 115 ልዩ ልዩ የመገናኛ ራዲዮኖች (23ቱ ለረጅም እርቀት ወይም በትከሻ የሚታዘሉ)፤ የጦር መሣሪያዎች፣ 67 የስልክ ግንኙነቶችን ለመጥለፍ የሚያችል መሣሪያ፣ ከአንድ ግለሰብ ላይ 350 ሲም ካርዶች፣ በተለያዩ ተቋማት ስም የተቀረጹ 6 ማሕተሞች፣ አንድ ግለሰብ በተለያየ ስም ያወጣው 7 ፓስፖርቶች መያዛቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጌቱ አርጋው ገልጸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ወንጀል የፈጸሙ 96 የጁንታው አባላትን አድኖ ለመያዝ የፍርድ ቤት ትእዛዝ ወጣ

የጁንታው ሕወሓት ቡድን አባላት

32ቱ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ናቸው

ኢዛ (ሐሙስ ኅዳር ፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 12, 2020)፦ የፌዴራል ፖሊስ የአገር ክህደት ወንጀል በፈጸሙ 96 የጁንታው ሕወሓት ቡድን አባላት ላይ የፍርድ ቤት ማዘዣ እንዳወጣባቸው አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዶክተር ደብረጽዮንን ጨምሮ 38 የሕወሓት አባላት ያለመከሰስ መብት ተነሳ

አቶ ጌታቸው ረዳ እና ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል

ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ በተለያዩ ወንጀሎች ይፈልጋቸዋል

ኢዛ (ሐሙስ ኅዳር ፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 12, 2020)፦ የቀድሞ የትግራይ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤልን ጨምሮ 38 የሚኾኑ የሕወሓት አባላትና ሌሎች ግለሰቦች ያለመከሰስ መብታቸው እንዲነሳ ተወስኗል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በአዲስ አበባ ቦንብ ፈንድቶ አንድ ግለሰብ ላይ ጉዳት ደረሰ

የአዲስ አበባ ታክሲዎች

የሕገወጡ ሕወሓት ቡድን ተላላኪዎች በመዲናዋ የጥፋት ተግባር ለመፈጸም ያዛጋጇቸው የጦር መሣሪዎች ተይዘዋል

ኢዛ (ረቡዕ ኅዳር ፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 11, 2020)፦ በአዲስ አበባ አድዋ ድልድይ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ዛሬ ጠዋት ቦምብ ፈንድቶ በአንድ ግለሰብ ላይ ጉዳት መድረሱን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሕወሕት ታጣቂዎቹን የኤርትራ መከላከያ መለዮ በማልበስ “ኤርትራ ወራናለች” እያለ ነው

M. Gen. Mohammed Tessema

መለዮውን ያመረተው በአልመዳ ጨርቃ ጨርቅ ነው

ኢዛ (ረቡዕ ኅዳር ፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 11, 2020)፦ ሕወሓት የኤርትራ መከላከያ ሠራዊትን መለዮ በአልመዳ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ በማምረትና ላደራጃቸው ታጣቂዎች በማልበስ፤ “ኤርትራ ወራናለች” በማለት ሕዝቡን እያደናገረ መኾኑን የመከላከያ ሠራዊት የኢንዶክትሪኔሽን ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጄኔራል መሐመድ ተሰማ ዛሬ አስታወቁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ