በትግራይ ሕግ የማስከበሩ ዘመቻ የመጨረሻ ምዕራፍ ተጀመረ

PM Abiy Ahmed

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመጨረሻውን ምዕራፍ ለማስፈጸም ለሠራዊቱ ትእዛዝ መሰጠቱን አስታወቁ

ኢዛ (ሐሙስ ኅዳር ፲፯ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 26, 2020)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በትግራይ ክልል የሕግ ማስከበር ዘመቻው የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ መኾኑንና የተሰጠው የ72 ሰዓታት ጊዜ በመጠናቀቁ የመከላከያ ሠራዊቱ የመጨረሻውንና ሦስተኛውን ምዕራፍ እንዲፈጸም ትእዛዝ መሰጠቱን አስታወቁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በማይካድራው ጭፍጨፋ የተገደሉት ከ600 በላይ እንደኾኑ ኢሰመኮ ገለጸ

The Ethiopian Human Rights Commission (EHRC)

የማይካድራው ጭፍጨፋ የግፍና የጭካኔ ወንጀል መኾኑን ኢሰመኮ ይፋ አደረገ
ጨፍጫፊዎቹ ለይተው ያጠቁት “አማራ” እና “ወልቃይቴዎች” ያሉዋቸውን ነው

ኢዛ (ማክሰኞ ኅዳር ፲፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 24, 2020)፦ በትግራይ ክልል ምዕራባዊ ዞን በምትገኘው የማይካድራ ከተማ በሲቪል ሰዎች ላይ በተፈጸመው ጭፍጨፋ ሕይወታቸውን ያጡት ዜጎች ከ600 በላይ መኾናቸውንና ድርጊቱ የግፍና ጭካኔ ወንጀል መኾኑን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ዛሬ ማክሰኞ ኅዳር 15 ቀን 2013 ዓ.ም. ባወጣው የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በአድዋ ተንቤን መስመር የሕወሓት አንድ ክፍለ ጦር ተደመሰሰ

State of Emergency Fact Checking

መከላከያ ሠራዊቱ ወደ መቀሌ የሚያደርገውን ግስጋሴ አጠናክሮ ቀጥሏል

ኢዛ (እሁድ ኅዳር ፲፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 22, 2020)፦ የአገር መከላከያ ሠራዊት በአድዋ ተንቤን መስመር ማይቅናጥል በተባለውና ልዩ ስሙ ሰላስል በተሰኘው የሐውዜን ተንቤን መገንጠያ መንገድ የገጠመውን የጁንታውን ኃይል ድል እንዳደረገና የጁንታው አንድ ክፍለ ጦር መደምሰሱ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለሕወሓት የመጨረሻ ያሉትን ማስጠንቀቂያ ሰጡ

PM Abiy Ahmed in military uniform

መቀሌ ለከተመው የጁንታው ቡድን 72 ሰዓታት ተሰጠው

ኢዛ (እሁድ ኅዳር ፲፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 22, 2020)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ሕግ የማስከበሩ ሥራ ሦስተኛውና የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ በመደረሱ፤ ለጁንታው ቡድን፣ ለሚሊሻውና ልዩ ኃይሉ የመጨረሻ ያሉትን ማስጠንቀቂያ ሰጡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የመከላከያ ሠራዊት እዳጋ ሐሙስ ከተማን ተቆጣጠረ

እዳጋ ሐሙስ

መከላከያ ሠራዊት መቀሌ ለመድረስ ጥቂት ቀርቶታል

ኢዛ (እሁድ ኅዳር ፲፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 22, 2020)፦ ከሰሞኑ ሽሬ፣ አክሱምና አዲግራት ከተሞችን ሙሉ ለሙሉ የተቆጣጠረው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ዛሬ እሁድ ኅዳር 13 ቀን 2013 ዓ.ም. ከአዲግራት ወደ መቀሌ የሚወስደው መንገድ ከመቀሌ በቅርብ ርቀት ላይ የምትገኘውን እዳጋ ሐሙስ ከተማን መቆጣጠሩ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲግራት ከሕወሓት ሙሉ ለሙሉ ነፃ ወጣች

TPLF and PM Abiy Ahmed

መከላከያ ሠራዊት ወደ መቀሌ እያመራ ነው

ኢዛ (ቅዳሜ ኅዳር ፲ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 19, 2020)፦ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ዛሬ አዲግራትን ከሕወሓት ኃይል ሙሉ ለሙሉ ነፃ ማውጣቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ይፋ አደረጉ። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመረጃ ማጣሪያ በበኩሉ “የመከላከያ ሠራዊታችን በአሁኑ ጊዜ ወደ መቀሌ እያመራ ነው” በማለት አስታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የመከላከያ ሠራዊት አክሱምን ሙሉ ለሙሉ፣ አድዋና የአዲግራት ዙሪያን ተቆጣጠረ

Members of the Tigray region special police force parade during celebrations marking the 45th anniversary of the launching of the “Armed Struggle of the Peoples of Tigray” in Mekelle, Ethiopia, on Feb. 19. MICHAEL TEWELDE/AFP VIA GETTY IMAGES

የሕወሓት ጁንታ ተዋጊዎች እና ከድተው ከጁንታው ጋር አብረው የነበሩ እጅ ሰጡ

ኢዛ (ዓርብ ኅዳር ፲፩ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 20, 2020)፦ የአገር መከላከያ ሠራዊት አክሱምን፣ አድዋ እና አዲግራት ዙሪያን መቆጣጠሩንና በርካታ የጁንታው ተዋጊዎችና ከጁንታው ጋር አብረው መከላከያ ሠራዊቱን ሲዋጉ የነበሩ ወታደሮች እጃቸውን እንደሰጡ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሠራዊቱ ወደ መቀሌ እየገሰገሰ ነው

State of Emergency Fact Checking

ጁንታው የሚመካባቸው የኮንክሪት ምሽጎች በመከላከያ ሠራዊት ፈርሰዋል

ኢዛ (ማክሰኞ ኅዳር ፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 17, 2020)፦ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ወደ መቀሌና አክሱም በድል አድራጊነት እየገሰገሰ መኾኑን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመረጃ ማጣሪያ ዛሬ ይፋ አድርጓል። ሽንፈት የተጎናጸፈው የሕወሓት ጁንታ ታጣቂዎች እየሸሹ እንደኾነ ተገልጿል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በመጨረሻም የጁንታው ሕወሓት የገንዘብ ምንጮች ደረቁ

EFFORT

ከ60 ቢሊዮብ ብር በላይ ካፒታል ያላቸው የሕወሓት ኩባንያዎች አካውንት ታገደ

ኢዛ (ማክሰኞ ኅዳር ፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 17, 2020)፦ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ውስጥ በሰፊው እጃቸውን አስገብተው ሲንቀሳቀሱ የቆዩና ከ60 ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል እንዳላቸው የሚታመኑት 34 የሕወሓት ኩባንያዎች የባንክ አካውንት ታገደ። የጁንታው ሕወሓት ቡድን የገንዘብ ምንጮች በስተመጨረሻ ደረቁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለመከላከያ ክብር እቆማለሁ!

ለመከላከያ ክብር እቆማለሁ!

በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ከመከላከያ ሠራዊቱ ጋር መቆማቸውን አስታወቁ

ኢዛ (ማክሰኞ ኅዳር ፰ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 17, 2020)፦ ለመከላከያ ክብር እቆማለሁ በሚል ዛሬ ማክሰኞ ኅዳር 9 ቀን ከጠዋቱ 5 ሰዓት ተኩል የተካሔደው ፕሮግራም በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ኢትዮጵያውያን በሚገኙበት አካባቢ ለመከላከያ ሠራዊቱ ያላቸውን ክብር በሚገልጹ ፕሮግራሞች ተካሒደዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ