ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እጅግ ታሟል

Temesghen Desalegn

ኢትዮጵያ ዛሬ (ማክሰኞ ታህሳስ ፲፰ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Dec. 27, 2016)፦ ሰሞኑን ያለበት ባለመታወቁና እስር ቤቶቹ ሁሉ ”አናውቅም” በማለታቸው ቤተሰቦቹን ጨምሮ ጉዳዩ ብዙዎችን አስጨንቆ የነበረው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፤ በመጨረሻ ዝዋይ እስር ቤት ቢገኝም፤ በአሁኑ ሰዓት እጅግ ታምሞ ሆስፒታል መግባቱ ታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የጀግናው አትሌት ሻምበል ምሩጽ ይፍጠር የፍትሐት ሥነሥርዓት ነገ ይፈጸማል

Miruts Yifter

ኢትዮጵያ ዛሬ (ሰኞ ታህሳስ ፲፯ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Dec. 26, 2016)፦ ባለፈው ኅሙስ ታህሳስ ፲፬ ቀን ፳፻፱ (Dec. 22, 2016) በሰባ ሁለት ዓመቱ ሕይወቱ ያለፈችው፣ የጀግናው አትሌት ሻምበል ምሩጽ ይፍጠር የጸሎተ ፍትሐቱ ሥነሥርዓት ነገ ማክሰኞ ታህሳስ ፲፰ ቀን (Dec. 27) ጠዋት አምስት ሰዓት ላይ ቶሮንቶ ካናዳ በሚገኘው ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን እንደሚፈጸም ለኢትዮጵያ ዛሬ ድረ ገጽ የደረሳት ዘገባ አስረዳ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝን ፍለጋ ቀጥሏል

Journalist Temesgen Desalegne

ኢትዮጵያ ዛሬ (ረቡዕ ታህሳስ 5 ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Dec. 14, 2016)፦ ላለፉት ስምንት ተከታታይ ቀናት ቤተሰቦቹ በአገሪቱ ውስጥ ባሉ ወህኒ ቤቶች ሁሉ ዞረው ሲፈልጉ ሰንብተዋል። አቤቱታቸውንም ለሚመለከተው ክፍል አሰምተዋል። ይሁን እንጂ ተመስገንን አየሁ የሚል አንድም የወህኒ ቤት አስተዳዳሪ አልተገኘም።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሰባት ኢትዮጵያውያን አስከሬኖች በጆንያ ተጠቅልለው በታንዛኒያ ወንዝ ውስጥ ተገኙ

7 Ethiopians killed in tanzaniaኢትዮጵያ ዛሬ (ማክሰኞ ታህሳስ ፬ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Dec. 13, 2016)፦ የሰባት ኢትዮጵያውያን አስከሬን በታንዛኒያ ወንዝ ውስጥ ተጥሎ መገኘቱን የአገሪቱ መንሥግት አስታወቀ። ኢትዮጵያውያኑ ወንዝ ውስጥ ሆን ተብለው የተጨመሩ መሆኑንም ፖሊስ ተናግሯል። አስከሬኖቹ በጆኒያ ከአሸዋ ጋር ተደርገው ነው ወደ ወንዝ የተወረወሩት ሲል ፖሊስ መግለጡን የኬንያ ቴሌቭዥኖች የዘገቡ ሲሆን፣ ሟቾቹ በሙሉ ወንዶች መሆናቸው ታውቋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በኢትዮጵያ ወህኒ ቤቶች ውስጥ 16 ያህል ጋዜጠኞች እንደሚገኙ ሲፒጄ አስታወቀ

CPJ imprisoned 2016

ኢትዮጵያ ዛሬ (ማክሰኞ ታህሳስ ፬ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Dec. 13, 2016)፦ በየዓመቱ በመላው ዓለም በሥራቸው ሳቢያ ብቻ ወደ ወህኒ ቤቶች የተወረወሩ ጋዜጠኞችን ቁጥርና ስም ዝርዝር ይፋ የሚያወጣው ዓለማቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተከራካሪው ድርጅት ሲፒጄ፤ ዛሬ ባወጣው ሪፖርት በኢትዮጵያ ወህኒ ቤቶች 16 ጋዜጠኞች መታጎራቸውን ይፋ አድርጓል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ ”የኦሮሞ እና የአማራ እውነተኛው የዘር ምንጭ” አዲስ መጽሐፍ በሦስት የአሜሪካ ከተሞች ተመረቀ

Prof. Fikre Tolossaአብርሃም ቀጄላ

የፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ ”የኦሮሞ እና የአማራ እውነተኛው የዘር ምንጭ” አዲስ መጽሐፍ በርካታ ኢትዮጵያውያን በተገኙበት በዩናይትድ ስቴትስ ኦፍ አሜሪካ ሦስት ከተሞች ተመረቀ። በሦስት ተከታታይ ቀናት ከዲሴምበር ፫ ቀን ጀምሮ በቨርጂኒያ፣ በዋሽንግተን ዲሲ እና በሜሪላንድ በሚገኙ የኢትዮጵያውያን ሬስቶራንቶች ነው ምርቃቱ የተካሄደው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የጋምቢያው ፕሬዝዳንት ያህያ ጃሜይ የምርጫውን ውጤት አልቀበልም አሉ

Adama Barrow and Yahya Jammeh

ኢትዮጵያ ዛሬ (ቅዳሜ ታህሳስ ፩ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Dec. 10, 2016)፦ ባለፈው ሣምንት በምርጫ መሸነፋቸውን በፀጋ መቀበላቸውን አሳውቀው የነበሩትና ጋምቢያን ላለፉት ሃያ ሁለት ዓመታት የመሩት የጋምቢያው ፕሬዝዳንት ያህያ ጃሜይ፤ በዛሬው ዕለት የምርጫውን ውጤት አልቀበልም አሉ። ድጋሚ ምርጫ መካሄድ አለበት ማለታቸው ተደመጠ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ፈይሳ ሌሊሳ ወደ ውድድር መድረክ ሊመለስ ነው

Feyisa Lelisa

ኢትዮጵያ ዛሬ (ቅዳሜ ታህሳስ ፩ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Dec. 10, 2016)፦ አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ ባለፈው ክረምት በሪዮ ዲጄኔሮ ኦሎምፒክ ማራቶን ውድድር ላይ የብር ሜዳሊያ ከመቀዳጀቱም በላይ በአገሩ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚታየውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት በመቃወም እጆቹን አጣምሮ በዓለም አደባባይ ላይ ካሳየ ወዲ የመጀመሪያው የሆነውን ውድድር ሊያደርግ በዝግጅት ላይ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝን አስሬአለሁ የሚል ወህኒ ቤት ጠፋ

Temesgen Desalegne

ኢትዮጵያ ዛሬ (ዓርብ ኅዳር ፴ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Dec. 9, 2016)፦ “ተመስገን ያለበትን ቦታ ለማወቅ ለ3ኛ ቀን ፍለጋ አንዳችን ወደ ዝዋይ፣ አንዳችን ወደ ሸዋ ሮቢት፣ አንዳችን ወደ ማዕከላዊ እስር ቤቶች እየሄደን ሲሆን፤ እናታችን ደግሞ ወደ ቤተክርስቲያን እየሄደች ነው።” ሲል ዛሬ ጠዋት የጋዜጠኛ ተመስገን ወንድም ታሪኩ ደሳለኝ በፌስቡክ ገጹ ቤተሰቡ ያለበትን ኹናቴ እና ያደረበትን ስጋት ገለጠ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ሰበር ዜና | የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ተስፋዬ ዲንቃ አረፉ

Former PM Tesfaye Dinkaኢትዮጵያ ዛሬ (ዓርብ ኅዳር ፴ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. Dec. 9, 2016)፦ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር፤ ብሎም ከ1981 እስከ 1983 ዓ.ም. በውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ኢትዮጵያን ያገለገሉት አቶ ተስፋዬ ዲንቃ ያዴሳ ኅዳር ፳፱ ቀን ፳፻፱ ዓ.ም. በ፸፯ ዓመታቸው አረፉ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ