አቶ ሀብታሙ አያሌው ወደ ውጭ ሔዶ ሊታከም ነው

(ቢቢኤን) ባለፈው ዓርብ ኅዳር 23 ቀን 2009 ዓ.ም. ከተከሰሰበት የሽብር ክስ በነጻ የተሰናበተው አቶ ሀብታሙ አያሌው ወደ ውጭ ሔዶ እንደሚታከም ገለጸ። የቀድሞ አንድነት ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ የነበረው አቶ ሀብታሙ፣ ሆሞሮይድ በተባለ በሽታ በጽኑ ሲታመም እንደሰነበተ ይታወቃል። ውጭ ወጥቶ ለመታከም በተደጋጋሚ ለፍርድ ቤት አመልክቶ በተለያዩ ሰበቦች ማመልከቻው ውድቅ ሲደረግበት የቆየው አቶ ሀብታሙ፣ በጠቅላይ ፍርድ ቤት ነጻ መባሉን ተከትሎ ውጭ ሔዶ ለመታከም ማቀዱን አስታውቋል።
ሙሉውን አስነብበኝ ...







(ኢሰመፕ) ፌስቡክ ላይ በጻፋቸው ጹሁፎች ምክንያት የሽብር ክስ ቀርቦበት ጉዳዩ በፍ/ቤት እየታየ የሚገኘውና በእስር ቂሊንጦ ያለው የቀድሞው የሰማያዊ ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዮናታን ተስፋዬ በሚገኝበት እስር ቤት ውስጥ ከአርብ ኅዳር 2/2009 ዓ.ም. ጀምሮ ቀንና ሌሊት በሰንሰለት ታስሮ እንደሚገኝ ታውቋል።


