አሊባባ በአዲስ አበባ
አሊባባ ግሩፕ በኤሌክትሮኒክስ የታገዘ ዓለም አቀፍ የንግድ መገናኛ ማዕከል ለመገንባት የሚያስችለውን ስምምነት ከኢትዮጵያ ጋር ተፈራረመ
ኢዛ (ሰኞ ኅዳር ፲፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. November 25, 2019)፦ በኤሌክትሮኒክስ ግብይት በዓለማችን ቀዳሚ ኩባንያዎች መካከል አንዱ የኾነው አሊባባ ኩባንያ ሊቀመንበር ጃክ ማ እና የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ መጀመሪያ በስዊዘርላንድ፣ ከዚያም በኋላ ሚያዝያ 2011 ዓ.ም. አጋማሽ ላይ በቻይና ተገናኝተው በጋራ ሊሠሩ በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ መክረው ነበር። በቻይና ሃንግዙ የሚገኝውን የአሊባባ ዋና መሥሪያ ቤት ጠቅላይ ሚንስትሩና የልዑካን ቡድናቸው በጃክ ማ አስጎብኝነት ተመልክተዋል። ስለኩባንያው አውግተዋል። በውይይታቸው መደምደሚያ ላይ አዲስ አበባ ለመገናኘት ቀን ቆርጠው ይለያያሉ።
ሙሉውን አስነብበኝ ...



