ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ ፓርላማ ይቀርባሉ

PM Abiy Ahmed

በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ይሠጣሉ ተብሎ ይጠበቃል

ኢዛ (ሰኞ ጥር ፳፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. February 3, 2020)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ጥር 25 ቀን 2012 ዓ.ም. ፓርላማ ቀርበው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ይሠጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ኢዜማ አገር አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲነት ሕጋዊ የሰውነት ማረጋገጫውን አገኘ

ኢዜማ

ሕጋዊ ሰርቲፊኬቱን የሠጠው ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነው

ኢዛ (ኀሙስ ጥር ፳፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. January 30, 2020)፦ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ - ፍትሕ ፓርቲ (ኢዜማ) አገር አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲ በመኾን ለመንቀሳቀስ የሚያስችለውንና ይህንኑ የሚያረጋግጥ የምዝገባና የሕጋዊ የሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተቀበለ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሐረር ከተማ መውጫና መግቢያ በቡድን በተደራጁ ወጣቶች ተዘግቶ ዋለ

Harar

የድሬ ዳዋ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ወደ ከተማዋ እንዳይገቡ ደንገጎ ላይ መንገድ ተዘጋባቸው

ኢዛ (ኀሙስ ጥር ፳፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. January 30, 2020)፦ በዛሬው ዕለት በሐረር ከተማና አካባቢው ሰዎች ከከተማ እንዳይወጡና እንዳይገቡ መንገድ የተዘጋባቸው ሲሆን፤ ወደ ድሬ ዳዋ ይጓዙ የነበሩ የድሬ ዳዋ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና ሌሎች ተጓዦች ከወደ አዲስ አበባ ሊገቡ ሲሉ ደንገጎ በሚባል ቦታ መንገድ ተዘግቶባቸዋል። ሐረር መሐል ከተማ የሚገኙ አብዛኞች ሱቆች ተዘግተው መዋላቸውን የከተማዋ ነዋሪዎች ለኢትዮጵያ ዛሬ ድረ ገጽ ገልጸዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአማራ ክልል የኢትዮጵያ ሕዝብ ከጐኑ እንዲቆም ጠየቀ

Protest in Amhara region over student abductions, January 28, 2020

ተማሪዎቹ ለታገቱበት ክልል ለኦሮሞ ሕዝብ ጥሪ አስተላልፏል

ኢዛ (ማክሰኞ ጥር ፲፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. January 28, 2020)፦ በደንቢ ዶሎ ተማሪዎች ላይ በተፈጸመው እገታና ጥቃት በአማራና በአማራ ተወላጅ ተማሪዎች ላይ ብቻ ሳይሆን፤ በሰብዓዊ ፍጡርና በዜጐች ላይ መኾኑን በመገንዘብ፤ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በተለይም ጥቃቱ የተፈጸመበት ክልል የኦሮሞ ሕዝብ ከጐናችን ይቁም ሲል የአማራ ክልል ብሔራዊ ክልል መንግሥት ዛሬ ጥር 19 ቀን 2012 ዓ.ም. አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የታገቱትን ተማሪዎች አስመልክቶ ከፍተኛ ሰላማዊ ሰልፍ በሃያ ዘጠኝ ከተሞች ተካሔደ

Protest in Amhara region over student abductions

“መንግሥት በእነዚህ ተማሪዎች እገታ ጉዳይ ላይ ግልጽ መረጃ ይሠጥ!”

ኢዛ (ማክሰኞ ጥር ፲፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. January 28, 2020)፦ ወደ ሁለት ወራት ለተጠጋ ጊዜ በእገታ ላይ መኾናቸው ሲገለጽ የቆዩትን የደንቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን በተመለከተ እስካሁን ምንም ዐይነት መፍትሔ ባለመወሰዱ በአማራ ክልል ባህር ዳርን ጨምሮ በሃያ ዘጠኝ ከተሞች ዛሬ ጥር 19 ቀን 2012 ዓ.ም. ከፍተኛ ሰላማዊ ሰልፍ ተደረገ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቦሌ ላይ ኮሮና ቫይረስ ይዟቸዋል ተብለው የተጠረጠሩ አራት ኢትዮጵያውያን ክትትል እየተደረገላቸው ነው

Coronavirus at Bole international airport

ለተጨማሪ ምርመራ የደም ናሙናቸው ወደ ደቡብ አፍሪካ ተልኳል

ኢዛ (ማክሰኞ ጥር ፲፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. January 28, 2020)፦ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ከቻይና ዉሃን ከተማ ወደ ኢትዮጵያ ሲገቡ የነበሩ አራት ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች በኮሮና ቫይረስ ተጠርጥረው በኳራንቲን ተለይተው ሕክምና እየተከታተሉ እንደሚገኙና በደም ምርመራ ከአምስት ዐይነት የኮሮና ቫይረስ ነፃ መኾናቸው ቢረጋገጥም፤ የደም ናሙናቸው ወደ ደቡብ አፍሪካ መላኩ ዛሬ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቻይና አደገኛ ገዳይ በሽታ ገጠማት

ዉሃን ከተባለች የቻይና ግዛት የተነሳው ኮሮና ቫይረስ

ኢትዮጵያም ያሰጋታል ተባለ

ኢዛ (ዓርብ ጥር ፲፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. January 24, 2020)፦ ዓለማችን ተዛማችና በፍጥነት የሚተላለፍ የሰው ልጆች ገዳይ የኾነ በሽታ በተደጋጋሚ ገጥሟታል። ከነዚህ በሽታዎች ውስጥ ኤድስ፣ ኢቦላና ሳርስ የሚጠቀሱ ሲሆኑ፤ ከነዚህ ውስጥ ኤድስ የአጥቂነቱ ዕድሜ እየተራዘመ ሲሔድ ሌሎቹ ግን በቁጥር ስር ሊውሉ ወይም ሊጠፉ ችለዋል። በቅርቡ ደግሞ መነሻው ቻይና የኾነው ኮሮና ቫይረስ ዓለምን በሥጋት ወጥሯት ይገኛል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በእስክንድር ነጋ ይመራል የተባለው ፓርቲ ጊዜያዊ እውቅና ተሠጠው

ባልደራስ

ሦስት ፓርቲዎችም በተመሳሳይ ተመዝግበዋል

ኢዛ (ረቡዕ ጥር ፲፫ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. January 22, 2020)፦ በጋዜጠኛና አክቲቪስት እስክንድር ነጋ የሚመራው “ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ” ፓርቲና ሦስት ሌሎች ፓርቲዎች ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጊዜያዊ የምዝገባ ፈቃድ (ሰርቲፊኬት) እና ጊዜያዊ እውቅና እንደተሠጣቸው ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የሕወሓት ም/ሊቀመንበርና የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትሯ ከኃላፊነትቸው ተነሱ

ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር (ሞንጆሪኖ)

ሦስት አዳዲስ ሚኒስትሮች ተሹመዋል

ኢዛ (ረቡዕ ጥር ፲፫ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. January 22, 2020)፦ የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር በመኾን ከጥቅምት 6 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ ሲያገለግሉ በቆዩትና የሕወሓት ምክትል ሊቀመንበር የኾኑት ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር ምትክ አዲስ ሚኒስትር ተሾሙ። ለሁለት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶችም አዳዲስ ሚኒስትሮች ተሹመዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በጎንደር ለጥምቀት በዓል ለታዳሚዎች የተሰናዳ ርብራብ በመደርመሱ ጉዳይ ደረሰ

Gonder Timket 2020

አሥር ሰዎች ሕይወታቸውን ሲያጡ፣ ከመቶ አርባ ሰዎች በላይ ተጎድተዋል

ኢዛ (እሁድ ጥር ፲፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. January 20, 2020)፦ የጥምቀት በዓል በድምቀት ሲከበርባት የዋለው ጎንደር፤ በዓሉ በሚከበርበት ሥፍራ በጥንታዊው የአፄ ፋሲል ገንዳ አካባቢ ለበዓሉ ታዳሚዎች በአጣና ርብራብ የተሰናዳ ማረፊያ (ማማ) ተደርምሶ አሥር ሰዎች ሕይወታቸው ሲያልፍ፤ ከአንድ መቶ አርባ ሰዎች በላይ ጉዳት እንደደረሰባቸው ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ