በዛሬው መረጃ በሕክምና ላይ ከሚገኙት ተጠቂዎች ያገገሙት ቁጥር በልጧል

Total coronavirus cases in Ethiopia, 2020-05-01

በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተጠቁት ቁጥር 133 ደርሷል

ኢዛ (ዓርብ ሚያዝያ ፳፫ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. May 1, 2020)፦ የጤና ሚኒስቴር ዛሬ ባወጣው ሪፖርት በ24 ሰዓት የኮሮና ቫይረስ ምርመራ ከተደረገላቸው 913 ሰዎች ውስጥ፤ ሁለቱ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ በመገኘታቸው፤ በኢትዮጵያ በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር 133 መድረሱን ሲያመላክት፤ በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ የኮሮና ቫይረስ ተይዘው ከነበሩት ታማሚዎች ውስጥ በሕክምና ላይ ከሚገኙት ይልቅ ያገገሙት ቁጥር በልጧል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ዛሬ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በምርጫው መራዘም ላይ ይወያያል

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ምርጫ ቦርድ ምርጫውን በተመለከተ ያቀረበውን የውሳኔ ሐሳብ ላይ ይመክራል

የምርጫውን ጉዳይ ጨምሮ አምስት አጀንዳዎችን ያጸድቃል ተብሏል

ኢዛ (ሐሙስ ሚያዝያ ፳፪ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 30, 2020)፦ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስድስተኛውን አገራዊ ምርጫ ለማካሔድ የሚያስችል ሁኔታ ባለመኖሩ፤ ምርጫ 2012 በሰሌዳው መሠረት ምርጫውን ነኀሴ 23 ቀን 2012 ዓ.ም. ለማካሔድ እንደማይችል ባቀረበው የውሳኔ ሐሳብ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ መርምሮ ያጸድቃል ተብሏል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ራስዋን ንግሥተ ነገሥት ዘኢትዮጵያ በሚል የምትጠራዋን ግለሰብ ፖሊስ አሰራት

እኅተ ማርያም

60 ደላሎች ታስረዋል

ኢዛ (ረቡዕ ሚያዝያ ፳፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 29, 2020)፦ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ራስዋን “ንግሥተ ነገሥት ዘኢትዮጵያ” የሚል መጠሪያ በመስጠት ስትንቀሳቀስ የቆየችው እኅተ ማርያም በሚል መጠሪያ የምትታወቀው ግለሰብ ዛሬ ከመሸ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋለች።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

መንግሥት በምርጫ ጉዳይ አራት አማራጮችን በማቅረብ ከተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር እየመከረ ነው

PM Abiy Ahmed

ሲቪክ ማኅበራትም በውይይቱ ተሳትፈዋል

ኢዛ (ረቡዕ ሚያዝያ ፳፩ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 29, 2020)፦ በኮሮና ወረርሽኝ ሳቢያ የተራዘመውን ስድስተኛውን አገራዊ ምርጫን (ምርጫ 2012) ለማካሔድ አስቸጋሪ በመኾኑ፤ መንግሥት አራት የመፍትሔ ሐሳቦችን በማቅረብ ከተፎካካሪ ፓርቲዎችና ሲቪክ ማኅበራት ጋር ውይይት በማካሔድ ላይ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

እስክንድር ነጋ ታስረው ተፈቱ

Eskinder Nega

በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ቤታቸው የፈረሰባቸው ድሆችን ሲጎበኙ ነበር

ኢዛ (ቅዳሜ ሚያዝያ ፲፯ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 25, 2020)፦ የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፕሬዝዳንት አቶ እስክንድር ነጋ ዛሬ ጠዋት ቅዳሜ ሚያዝያ 17 ቀን በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን የፓርቲው አመራሮች ገልጸዋል። ከምሽቱ ሦስት ሰዓት አካባቢ ተፈትተዋል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአስቸኳይ ጊዜውን አዋጅ ጥሰው የሠረጉት ሕግ አስከባሪ በቁጥጥር ሥር ዋሉ

ፖሊስ

“ካልሰማህ ሕግ ተፈፃሚ ይኾንብሃል!”

ኢዛ (ሐሙስ ሚያዝያ ፲፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 23, 2020)፦ ይህ ዜና የተሰማው ከአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ዲማ ወረም ወረዳ ነው። ወቅታዊውን የኮሮና ቫይረስ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በመጣስ በተፈፀመ ሕግ መተላለፍ አንድ ሰው በቁጥጥር ሥር ውሎ መታሰሩን ያመለክታል። ሕግ ጥሷል ተብሎ በሕግ ጥላ ሥር የሚገኘው ሰው ደግሞ ሕግ አስከብር ተብሎ ኃላፊነት የተሠጠው ሰው ነው። ፖሊስ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ከአክሱም ለይቶ ማቆያ ሊያመልጥ ሲል የተያዘ ግለሰብ የስድስት ወር እስራት ተፈረደበት

Axum

ኢዛ (ማክሰኞ ሚያዝያ ፲፫ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 21, 2020)፦ በትግራይ ክልል በአክሱም ከተማ በለይቶ ማቆያ ማዕከል ውስጥ ገብቶ የነበረ አንድ ግለሰብ፤ ከለይቶ ማቆያው ሊያመልጥ ሲል መያዙንና የስድስት ወር እስራት እንደተፈረደበት ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 96 ደረሰ

Total coronavirus cases in Ethiopia, 2020-04-17

ከአራቱ አዳዲስ በቫይረሱ ከተያዙት ውስጥ አንዱ ከዱባይ የመጣ ነው

ኢዛ (ዓርብ ሚያዝያ ፱ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. April 17, 2020)፦ ባለፉት 24 ሰዓታት 842 ሰዎችን በመመርመር አራት አዳዲስ የኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎች መገኘታቸውን በኢትዮጵያ በቫይረሱ የተገኘባቸውን ሰዎች ቁጥር 96 አድርሶታል። ከአራቱ አዳዲስ በቫይረሱ ከተያዙት ውስጥ አንዱ ከዱባይ የመጣ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ