ተጠባቂው የሁለቱ ምክር ቤቶች ስብሰባ ዛሬ ከሰዓት በኋላ ይካሔዳል

TPLF

የሕወሓት አባላት ይገኛሉ ወይስ አይገኙም የሚለው በጉጉት እየተጠበቀ ነው

ኢዛ (ሰኞ መስከረም ፳፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. October 5, 2020)፦ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት የጋራ ስብሰባቸውን ዛሬ ሰኞ መስከረም 25 ቀን 2013 ዓ.ም. ከቀትር በኋላ ያካሒዳሉ። የሕወሓት የሁለቱም ምክር ቤቶች አባላት በስብሰባው ላይ ይገኛሉ ወይስ አይገኙም የሚለው በጉጉት እየተጠበቀ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የደመራ በዓል በአዲስ አበባና በተለያዩ የአገሪቱ ከተሞች እየተከበረ ይገኛል

የደመራ በዓል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ሲከበር

በመስቀል አደባባይ ከ5-6 ሺህ ታዳሚዎች ተገኝተዋል

ኢዛ (ቅዳሜ መስከረም ፲፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 26, 2020)፦ የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ ከተማ በመስቀል አደባባይ እየተከበረ ነው። ሐረርን ጨምሮ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች በዓሉ እየተከበረ ይገኛል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የአርቲስት ሐጫሉን ግድያ ተከትሎ በተፈጸሙ ወንጀሎች ምርመራ ተጠናቀቀ

Fekadu Tsega (L) and Husen Osman (R)

የፌዴራልና የኦሮሚያ ዓቃቤ ሕጎች በ5,728 ግለሰቦች ላይ ክስ መመሥረታቸው ተገለጸ
በኹከቱ የወደመ ንብረት 4.7 ቢሊዮን ብር ነው
በሐረር ሐውልት ያፈረሱ በሽብር ሕጉ ይጠየቃሉ

ኢዛ (ቅዳሜ መስከረም ፲፮ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 26, 2020)፦ ከአርቲስት ሐጫሉ ሁንዴሳ ግድያን ተከትሎ በተፈጸሙ ወንጀሎች ዙሪያ በኦሮሚያ ክልል ሲያካሒድ የነበረውን ምርመራ ዓቃቤ ሕግ ማጠናቀቁንና በወቅቱ በተፈጸሙ ጥቃቶች 4.67 ቢሊዮን ብር ግምት ያለው ንብረት መውደሙን ገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አርቲስት አልማዝ ኃይሌ አረፈች

Almaz Haile

ሥርዓተ ቀብሯ ነገ ይፈጸማል

ኢዛ (ዓርብ መስከረም ፲፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 25, 2020)፦ ከ42 ዓመታት በላይ በሞያዋ መልካም ሥም ያተረፈችው ታዋቂዋ አርቲስት አልማዝ ኃይሌ ዛሬ ዓርብ መስከረም 15 ቀን 2013 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች። ባለፈው መስከረም 1 ቀን 2013 ዓ.ም. የ75ኛ ዓመት የልደት በዓልዋ ተከብሮላት ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

በቤንሻንጉል ጉሙዝ በዳግመኛ ጥቃት የንጹኀን ሕይወት አለፈ

Benishangul Gumuz

የሰብአዊ መብት ኮሚሽን 15 ሰዎች መገደላቸውን አረጋግጫለሁ አለ

ኢዛ (ዓርብ መስከረም ፲፭ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 25, 2020)፦ በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን፣ ዳንጉር ወረዳ፣ ማንቡክ ከተማ በንገዝ ወንዝ አካባቢ በሚገኝ መንደር ዛሬ ከንጋቱ 10 ሰዓት አካባቢ ዳግመኛ ጥቃት ተሰንዝሮ ከ15 - 20 የሚኾኑ ንጹኀን ሕይወታቸው መቀጠፉ ተገለጸ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የምክትል ኤታማዦር ሹሙ ማስጠንቀቂያ

Gen. Berhanu Julla

በኃይል ፍላጎቴን አሳካለሁ በሚል ማናቸውም አካል ላይ እርምጃ ለመውሰድ እንገደዳለን አሉ

ኢዛ (ሐሙስ መስከረም ፲፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 24, 2020)፦ ሕገ መንግሥቱን በጣሰ መልኩ በኃይል ፍላጎቴን አሳካለሁ በሚል የትኛውም አካል ላይ እርምጃ ለመውሰድ የሚገደዱ መኾናቸውን ምክትል ጠቅላይ ኤታማዦር ሹሙ ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ አስታወቁ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

ለአቶ ልደቱ የተፈቀደው ዋስትና ታገደ

Lidetu Ayalew

ዋስትናውን ያገደው የኦሮሚያ ጠ/ፍ/ቤት ምሥራቅ ሸዋ ተዘዋዋሪ ምድብ ችሎት ነው

ኢዛ (ሐሙስ መስከረም ፲፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 24, 2020)፦ ያልተፈቀደ የጦር መሣሪያ በመያዝ ወንጀል በምሥራቅ ሸዋ ዞን ክስ የተመሠረተባቸውና ከትናንት በስቲያ (ማክሰኞ መስከረም 12 ቀን 2013 ዓ.ም.) በ100 ሺህ ብር ዋስትና እንዲለቀቁ የተፈቀደላቸው አቶ ልደቱ አያሌው የተሰጣቸው የዋስትና ፈቃድ ታገደ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አቶ ልደቱ በአስቸኳይና ያለምንም ቅድመ ሁኔት ይፈቱ ሲሉ የሰብአዊ መብት ኮሚሽነር አስታወቁ

Lidetu Ayalew (L), Ethiopian Human Rights Commission (M), Dr. Daniel Bekele (R)

“አላስፈላጊ እስር ማስቀረትና የሰብአዊ መብት ይከበር!” ዶ/ር ዳንኤል በቀለ

ኢዛ (ሐሙስ መስከረም ፲፬ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 24, 2020)፦ በፍርድ ቤት ውሳኔ በ100 ሺህ ብር ዋስ ከእስር እንዲፈቱ የተወሰነላቸው አቶ ልደቱ አያሌው፤ ያለምንም ቅድመ ሁኔት ከእስር መፈታት እንዳለባቸው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ አሳሰቡ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የመስቀል ደመራና የኢሬቻ በዓላት ላይ ያለ ይለፍ መታደም እንደማይቻል ተገለጸ

አቡነ ማቲያስ

ፓትሪያርኩ ደመራ ከአምስት ሺህ ባልበለጡ ሰዎች ይከበራል አሉ

ኢዛ (ረቡዕ መስከረም ፲፫ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. September 23, 2020)፦ በመስቀል ደመራና በኢሬቻ በዓል ላይ ይለፍ ያልያዘ እንደማይታደምና የበዓሉ ተሳታፊ የሚኾኑ ባጅ የተሰጣቸው ብቻ መኾኑን ፖሊስ አስታወቀ።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ