የጎንደር ጦርነት የአርበኞች ድል የፋሽስት ጣልያን የመጨረሻ ውድቀት

ኃብተሥላሴ ስለሺ (ጌቱ) ከፓሪስ - ፈረንሣይ

ወራሪው የፋሽስት ጣልያን ጦር በጀግኖች አርበኞች ተጋድሎና በእንግሊዝ ረዳትነት ሚያዝያ ፳፯ ቀን ፲፱፻፴፫ ዓ.ም. ድል ሆኖ አዲስ አበባን ከለቀቀ በኋላ፤ የተቀረው የጠላት ጦር የምስራቅ አፍሪካ የጣልያን ጦር የበላይ አዛዥ በሆነው በዱክ ዲዎስታ አመራር ስር ደሴ ላይ መሽጎ ሲጠባበቅ፤ የቀረው ጦር እንዲሁ የምስራቅ አፍሪካ ምክትል ጦር አዛዥ በሆነው በጄኔራል ናዚ አመራር ጎንደር ላይ መሽጎ የሙሶሎኒን እርዳታ ይጠባበቅ ነበር።

ይሁንና ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ በድል አዲስ አበባ ከገቡ በኋላ አርበኛው እንደቀደመው ከእንግሊዝ ጦር ጋር በመተባበር የጠላትን ጦር እየደመሰሰ አዲስ አበባ በድል እንደገባ ሁሉ፤ አሁንም በየሀገሩ መሽጎ የተቀመጠውን የጠላት ጦር ከእንግሊዝ ጦር ጋር በመተባበር እንዲደመስስ ትዕዛዝ ሰጡ። በተለይም በደሴ እና በጎንደር መሽጎ የተቀመጠውን የዱክ ዳዎስታንና የጄኔራል ናዚን ጦር እንዲደመስሱ ከግርማዊነታቸው የተሰጣቸውን ትዕዛዝ ተቀብለው ደጃዜማች ኃብተሥላሴ በላይነህ አርበኞቻቸውን ይዘው ወደ ሰሜን ዘመቱ። ... (ሙሉውን ጽሑፍ በፒ.ዲ.ኤፍ. አስነብበኝ!

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ