የረቡዕ ግጥም ፴፱
”ግልፅ ነው ይሄ ሰው የግንባር ላይ ሥጋ
እውነትን አፍረጥራጭ ጨርሶ ሳይሰጋ”
በማለት ብዙ ሰው ይችላል ሊያደንቅህ
ወይም ባፉ ብቻ ሸነጋግሎ ሊያልፍህ
እኔ ግን አጥብቄ እናገርሃለሁ
ሁሉንም አትዘርግፍ ብዬ እመክርሃለሁ
ወለላዬ ከስዊድን (This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.)



