አልነጋም- ገና ነው!

ዳግማዊ ዳዊት This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.

የሰማይ ኮርኒሥ ሆኖ - ማቅ የመሰለ ደመና

ከታችም አውሎ ነፋስ - ፉጨቱን እያሰማ

አቧራውን አስነስቶ - ዛፍ ቅርንጫፉን እያሾረ

ዛሩ እንደወረደ ባለአውሌ - አለመጠን እያስጨፈረ

ዓይን ቢወጉ በማያሳይ - ጥቅጥቅ ባለ ጨለማ

ወዴት ነው መድረሻችን - ጉዟችን የሚያቀና?

 

ትናንት እንዳስቆመን ዝናብ - ሊዘንብ ሰማዩ አግቶ

ወዴት ነው የምንሄደው - በትናንቱ ምን ታይቶ?

 

ትርምስምሳችን ወጥቶ - ጨቅይቶ ሳለ መንገዱ

ለይምሰል አይሆንም ወይ - ደግመን ዛሬ መሄዱ?

 

ትናንት መካሪ ጠፍቶ - ሌሊቱ ገና እንዳልነጋ

ጉዞው መርዛም - እሾክ በዝቶበት - ስንቱ ነው የተወጋ?

 

እኔስ አልምክርውም- የዛሬውን መንገድ

እስኪነጋ እቆያለሁ - ካልሆነብኝ የግድ

አልነጋም ገና - ጨለማ ነው ሌሊት

እነሱንም ንገሩዋቸው - መጓዙን ይተዉት

ተከታያቸውን በመሉ - የአውሬ ቀለብ አያርጉት።


ዳግማዊ ዳዊት

This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.

ጥር 2002 ዓ.ም.

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ