ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ አዲስ አበባ ገብተዋል
ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ
ሁለት ቀን ይቆያሉ
ኢዛ (እሁድ ሚያዝያ ፳፭ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. May 3, 2020)፦ ከሰሞኑ በአንዳንድ የማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ ሕይወታቸው ስለማለፉ በተደጋጋሚ ሲንገርባቸው የነበሩት የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ አዲስ አበባ ገብተዋል።
ዛሬ እሁድ ሚያዝያ 25 ቀን አዲስ አበባ የገቡት ፕሬዝዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ፤ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠቅላይ ዐቢይ አሕመድ ጋር በተለያዩ ወቅታዊ ጉዳዮች ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል። ቆይታቸውም ለሁለት ቀን መኾኑም ተጠቅሷል። (ኢዛ)



