Ethiopian Airlines

የኢትዮጵያ አየር መንገድ

ወደ ደሴ የሚያደረገው በረራ መስተጓጎሉ ተገለጸ

ኢዛ (ማክሰኞ መጋቢት ፯ ቀን ፳፻፲፪ ዓ.ም. March 17, 2020)፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአየር ፀባይ ምክንያት ተስተጓጉሎ የነበረውን የመቀሌ፣ የባህር ዳር፣ የላሊበላ፣ የጐንደር፣ የሁመራ፣ የአክሱምና የሽሬ በረራዎች መልሶ መጀመሩን አስታውቋል።

አየር መንገዱ የካቲት 6 ቀን 2012 ዓ.ም. ወደ እነዚህ ከተሞች የነበረውን በረራ በአየር ፀባይ ምክንያት አቁሞ የነበረ ሲሆን፤ ትናንት መጋቢት 7 ቀን 2012 ዓ.ም. ግን መልሶ መጀመሩን ገልጿል። ወደ ደሴ ያደርግ የነበረው በረራ ግን መታጐሉን የገለጸው አየር መንገዱ የአየር ፀባዩ እንደተስተካከለ የደሴውም በረራ ይቀጥላል ብሏል። ለተፈጠረው ችግም አየር መንገዱ ይቅርታ ጠይቋል። (ኢዛ)

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ