የኢትዮ - ካናዳውያን የዲሞክራሲ ፎረም በኦታዋ - ካናዳ

የድጋፍ መግለጫ

 

በጄነራል ከማል ገልቹ የሚመራው የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ለበርካታ የትግል ዓመታት ያራምድ የነበረውን ከኢትዮጵያ የመገንጠል አ ንዳን በመተው ለሁሉም የኢትዮጵያ ዜጐች መብት ፤ እኩልነትና ነፃነት መከበር እታገላለሁ በማለት ታህሳስ 22 ቀን 2004 ዓም ያወጣውን መግለጫ የኢትዮ ካናዳውያን የዲሞክራሲ ፎረም በኦታዋ - ካናዳ በደሥታ የተቀበለው መሆኑን ይገልፃል።


ፎረማችን በአገራችንና በህዝባችን ላይ የወደቀውን የግፍ አገዛዝ በማስወገድ በምትኩ አገራዊ አንድነቷ የተጠበቀ፤ የህዝቧ እኩልነትና የህግ የበላይነት የተረጋገጠባት ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ለመመስረት በሚደረገው ትግል ውስጥ የትግሉ አካል በመሆን የሚጠበቅበትን የዜግነት ግዴታ ለመወጣት በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል።


በመሆኑም ፎረማችን የአገርና የህዝብ ጠላት የሆነውን ህውሃት/ኢህአዴግ በኢትዮጵያችን ውስጥ እያደረሰ ያለውን ዘርፈ ብዙ ግፍና በደል በተለያዩ መድረኰች አጋልጠናል ፤ ኢትዮጵያን ለመታደግ በአንድነት ጥላ ሥር በመሰባሰብ ላይ ያሉትን የፖለቲካ ድርጅቶች ፤ ሲቪክ ማህበራትና ታዋቂ ግለሰቦችን ያካተተ አንድ ጠንካራ ህብረት እንዲመሰረት የሚደረገውን ጥረት በመደገፍ አስፈላጊውን ድጋፍ ሁሉ ለመስጠት ይህ ፎረም ቃል ይገባል።


በማከልም ይህንን በጄነራል ከማል የቀረበውን የኢትዮጵያዊነትን ጥሪ ባለመቀበል በተፃራሪነት የቆሙ የፖለቲካ ድርጅቶች በኢትዮጵያውያን ህብረት ላይ የሚያካሄዱትን አሉታዊ ቅስቀሳ በመተው አቋማቸውን አስተካክለው ህዝባዊውን እንቅስቃሴ እንዲቀላቀሉ ጥሪያችንን እናቀርባለን።


ፎረማችን አሁንም እነ  ነራል ከማል የወሰዱትን አቋም ከልብ እየደገፈ ጊዜው የግድ የሚለውን የጋራ ትግል እንዲ ምሩልን አደራ እንላለን።


ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር !

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ