ቪቫ ኢትዮጵያ! ቪቫ ምኒልክ!

ቪቫ ኢትዮጵያ! ቪቫ ምኒልክ!Adwaየአድዋው ድል
ሰሎሞን ተሰማ ጂ. 

የዐድዋ ጦርነት እስከዛሬ በአፍሪካም ምድርና በአፍሪካ ታሪክ ከተከናወኑት ጦርነቶች ከፍተኛውን የዋጋና የክብር ድልድል የያዘ ጦርነት ነው። አኒባል የአልፕን ተራሮች ዞሮ የአውሮፓን ኃያል መንግሥት ካሸነፈ ወዲህ፣ አንድ አውሮፓዊ ጦር በአፍሪካውያን ጦር ሲሸነፍ ለመጀመሪያ ጊዜ ነበር። ስለሆነም፣ ጦርነቱ ብዙ መልክና ብዙ ቅጽል ተሰጥቶታል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አስሩ የጽልመት ቀናት በኢትዮጵያ

(ከየካቲት 8/1929 - የካቲት 17/1929 ዓ.ም)

ሰሎሞን ተሰማ ጂ.

በመስከረም 1927 ዓ.ም የወጣው Detroit Times — (Sept. 22, 1935, p. 3) መጽሔት ከአንድ ታላቅ ሳይቲስትና የፈጠራ ባለሙያ ጋር የኢትዮጵያንና የጣሊያንን ወረራ አስመልክቶ ቃለ-ምልልስ አድርጎ ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

“የኢትዮጵያና የሕዝቧ ደመኛ ...” ይሰቀል!

ብ/ጄኔራል መንግሥቱ ነዋይ (ግራ)፣ ገርማሜ ነዋይ (ቀኝ) Mengistu and Germame Newayሰሎሞን ተሰማ ጂ.

በ1900 ዓ.ም. በኢትዮጵያና በፈረንሳይ መንግሥታት ስምምነት፣ “በልዩ የቆመ ፍርድ ቤት” የሚል ስያሜ የተቋቋመ ፍርድ ቤት ነበር። ፍርድ ቤቱ የመጀመሪያ ሥራውን በ1914 ዓ.ም. ሲጀምር፣ የመጀመሪያው የፍርድ ቤቱ ፕሬዝዳንት ሆነው የተሾሙት ብላቴን ጌታ ሕሩይ ወልደ ሥላሴ ነበሩ። ከርሳቸውም ቀጥለው የተሾሙትም ነጋድራስ አፈወርቅ ገብረየሱስ ናቸው። የዚህ ፍርድ ቤት ዋነኛው ተግባር የውጭ ዜጎች እርስ-በራሳቸው ሲጋጩና/ወይም የውጭ አገር ዜጎችና ኢትዮጵያውያን በተጋጩ ወይም በተካሰሱ ጊዜ ፍርድ መስጠት ነበር።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የፊደል ጣጣና የአምስቱ ትውልድ ውዝግብ!

ሰሎሞን ተሰማ ጂ.

ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፣ “መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ” (1948) በታተመው መጽሐፋቸው ውስጥ እንደበየኑት፣ “ፊደል ማለት ቀለም፤ ምልክት፤ የድምፅና የቃል መልክ፤ ሥዕል፤ መግለጫ ማስታወቂያ፤” ነው (ገጽ 616)። ደስታ ተክለ ወልድም በበኩላቸው፣ በ1962 ዓ.ም. ባሳተሙት “ዐዲስ ያማርኛ መዝገበ ቃላት” መጽሐፋቸው እንደገለጹት፣ “ፊደል ማለት የነገር፣ የቃል ምልክት፣ የድምፅ ሥዕል፣ ማጉሊያ፤ መግለጫ ነው፤” (ገጽ 988)። በሁለቱም ሊቃውንት አተያይ ውስጥ ፊደል የድምፅና የቃል ምልክት መሆኑን በአጽንዖት ተገልጧል።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

የፊደል የት መጣነት

ካሣሁን ዓለሙ

”ወርቅ ነው፤ ወርቅ ነው የግዕዝ ፊደል፣

ሰባት እጅ የጠራ በሰባት ባሕል።” አለቃ ኪዳነወልድ ክፍሌ

የሰውን ልጅ ዕውቀት ታሪካዊ ዕድገት ስንዳስሰው የጽሑፍ ምልክትን በመፍጠር ጀምሮ አሁን ያለንበት የመረጃ ዘመን ላይ ደርሷል። ከጥንቱ የጽሑፍ ምልክት ፈጠራ አንጻር ስንገመግምም በአሁን ጊዜ ያለው የዕውቀት ደረጃ ብዙም ሊለፈፍለት የማይገባ ይመስላል። ምክንያቱም የጥንቱ ለመጀመር የተደረገ ጥረት ነው፤ የአሁኑ ዕውቀት ደግሞ ያለውን ማስፋፋትና ማጎልመስ ነው።

ሙሉውን አስነብበኝ ...

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ