ሉሉ ከበደ (ጋዜጠኛና ደራሲ)

ውድ አንባቢያን ወደ ዋናው ጉዳይ ከመሄዴ በፊት ልጠቁም የምፈልገው ነገር የማቀርባቸውን ጽሁፎች በተመለከተ የምትጽፉልኝን አስተያየቶች፤ ትችቶችን አጠቃለው ሁሉንም በጥሞና አነባቸዋለሁ። እናም ሁላችሁንም ከልቤ ሳላመሰግን አላልፍም። ትችት ያስተምራል። የድጋፍም ሀሳብ ያስተምራልም ያበረታታልም። ሁለቱም እኩል ይጠቅማሉ። ወደፊት ከምትልኩልኝ መልሶች አለፍ አለፍ እያልኩ አጠር አጠር ያሉትን ሁለቱን ላንባቢያን አቅርቤ ወደምናገረው ነገር አልፋለሁ። ከዛሬ ልጀምርና “አያልቅበት .. “ ለሚለው ከደረሱኝ አስተያየቶች ሁለቱን ተመልከቱና ወደ አቅርቦቱ እንሂድ።

 

Nebrom Senay

አንተ እከካም ጥፍራም አንተም ወንድ ሆንክና ሴትን ትንቅ ጀመርክ? ማናባትህ ነው ያ ጭራቅ አባትህን \ደርግን\ የነፋው?

Was it not the valianr female fighters of the valian TPLF/EPRDF? You must be a super fool to expect any one going to the bush and die for you senile, aged old man. You shall perish without seing the comfort at 4 killo. You cannot even talk ina convincing manner. You re too old to covet power. chaw chaw

                       …..                                                        

Bizunesh Gizaw

Hi comrade Lulu Kebede

I appreciate your artilce. It reflects the everyday atrocities commited by the Weyane regime. This is not a state leadership but a mafia that empowers itself at any cost at the expense of dying peoples of Ethiopia simply to rob the country. As you said, they do not have any ethics. any morality or any element of leading a nation with a national interest. Even Fascist Benito Musolini and Adolf Hitler had national interest. These are so wild and greedy that they have no comparison except beasts.

 

Now the other problem is that there are over hundred active parties, some that seem to represent the same group of people, but most parties follow one trend; that is to serve the divisive scheme of Weyane. That means there are also greedy apostles that simply run for individual or narrow group power while we all know and the Ethiopian country man knows that unity is the only power to eliminate those vultures. For heaven sake let us advocate all Ethiopians, irrespective of race, language, religion and what have to stand in unison under one organization first to eradicate these vultures. If we agree to create a common forum of eradicating them, I assure you that the same forum can live side by side by respecting local rights, that means creating the basis of a federal form of administration or government!!!. We have to dream of an ideal unity devoid of personalities that we envison, that is out of cult. Then we may be able to see a democratic and developed nation. Could it be?                                               

 

ለዛሬ ወደተነሳሁበት ጉዳይ እናልፋለን።                                                       

እንደ ኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር በ1983 ወያኔና ሻዕቢያ መላዋን ኢትዮጵያ ሲቆጣጠሩ፤ በየክፍለ ሀገሩ ከተሞች በገቡ ቁጥር የሕውሀት ሰራዊት ሁለተኛ ተግባር የነበረው ሁላችሁም አገር ቤት የነበራችሁ እንደምታስታውሱት፤ የመንግስትም፤ የህዝብም፤ የግለሰብም ንብረትና ሀብት እየዘረፉ፤ በሚያስገርም ፍጥነት ወደትግራይ ማሸሽ ነበር። በየባንኮቹ ይገኝ የነበረ የገንዘብና የወርቅ ክምችት፤ የሀብታም ግለሰቦች ትላልቅና ትናንሽ ተሽከርካሪዎች፤ የህዝብ ከሆኑ ነገሮች እሰከ ታች ቀበሌ ክበቦች ያለ ፍሪጅና ምግብ ማቅረቢያ ትሪ ሳይቀር፤ በፍጥነት እየዘረፉ በሚዘርፏቸው ካሚዎኖች እየጫኑ በፍጥነት ወደ ትግራይ እየወሰዱ መሸሸግ ነበር። ካሚዎኖች፤ ጀነሬተሮች፤ የእህል ወፍጮዎች፤ ቴሌቭዢኖች፤ ማናቸውም ዋጋ አላቸው ብለው የገመቱትን ቁሳቁስ ሁሉ፤ እንደ እብድ እየተክለፈለፉ ይሰበስቡ ያሻግሩ ነበር። በቀንም በጨለማም። ከጅማና ከደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ የደን ሀብት ዘረፋ አልቀረም። የአዲስ አበባ ሕዝብ ቋሚ ምስክር ነው፤ ሁላችሁም ታውቃላችሁ። ያኔ ማታማታ የጎዳና ላይ መብራት እንዲጠፋ እየተደረገ፤ ከባድ ተሽከርካሪዎች  ከነተጎታቾቻቸው ምን እንደሆነ ሳይታወቅ እጅግ ብዙ ነገር ተጭነው በብዛት እየተከታተሉ ከከተማው ሲወጡ ማየት በየማታው የተለመደ ነበር። 

 

ወራቶች እያለፉ ምንም የሚገታቸው ሀይል አለመኖሩንም አረጋግጠው ሁሉንም ነገር ተቆጣጥረው አንደመረጋጋት ሲሰማቸው፤ ከሻዕቢያ ጋር እየተሻሙ ንብረትና ሀብት ዘረፋው ሳያቋርጥ፤ በተቆጣጠሩት ቴሌቭዢንና ራዲዮ፤ ማስታወቂያ ማውጣት ጀመሩ። ሰርቀው የሰበሰቡትን እቃ ሕዝቡ መልሶ የራሱን ንብረት እንዲገዛቸው ወተወቱ። ይህን በመሰለ ሁኔታ የሀገሪቱንና የህዝቡን ሀብትና ንብረት መቆጣጠር መዝረፍ ቀጠለ። ከውጭ የሚመጡ እርዳታዎችንም ወደካዝናቸው ማስገባቱን ቀጠሉ። ቤተ እስራኤሎችን                       የእስራኤል መንግስት ከኢትዮጵያ ሲወስድ፡ ይከፈል የነበረውን 36 ሚሊዮን ዶላር አካባቢ ተቀብለው ወሰዱት። በወቅቱ በኢትዮጵያ የእስራኤል አንባሳደር የነበሩ ሰው ስማቸው ተዘንግቶኛል፤ ስለገንዘቡ ተጠይቀው አዲሱን መንግስት መጠየቅ እንደሚቻል ተናግረው ነበር።

 

ቢያንስ ለመጀመሪያዎቹ አምስት አመታት የሀገሪቱና የህዝብ የሆነ በቢሊዮን የሚቆጠር ብር በጃቸው አስገቡ።እቅዳቸው ያንን ገንዘብ በልዩ ልዩ ፈርጅ በመከፋፈል በሀገሪቱ ያለውን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ በሙሉ በሞኖፖል ይዞ የሚያንቀሳቅስ ንብረትነቱ የህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ግንባር የሆነ በማእከላዊ ኮሚቴው የሚመራ ግዙፍ የኢኮኖሚ አውታር መፍጠር ነበር። በእርሻ፤ በኢንዱስትሪ፤ በትራንስፖርት፤ በግንባታ፤ በአገልግሎት ሰጭነት፤ በውጭና በውስጥ ንግድ፤ በማናቸውም መስክ መላ ሀገሪቱን የሚሸፍን የንግድ አውታር መመስረት ነበር።ነባሩን የንግድ ህብረተሰብ፤ ነባሩን ባለሀብት ቀስ በቀስ እያከሰሩና እያዳከሙ፤ የሚቀሙበትንም ዘዴ እየፈለጉ ሁሉንም ከጨዋታ ውጭ በማድረግ ጥቂት የትግራይ ባለሀብቶችን በመፍጠር፤ እነሱን የበላይ አድርጎ፤ ህዝቡን ጭሰኛ በማድረግ የአገዛዙን ቀጣይነት ማረጋገጥ አቋማቸው ነበር።

 

አነሆ በዚህም ራእይ መሰረት እንደ ኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር በ1987 ዓም አካባቢ  በዘመቻ መልክ ስልሳ የሚሆኑ ትላልቅ የንግድ ኩባንያዎችና ድርጅቶች ከሶስት አስከ አራት ቢሊዮን በሚሆን የመነሻ ካፒታል ተቋቁመው ስራ ጀመሩ። ይህ ገንዘብ ስልጣኑን በተቆጣጠሩ አምስት አመት ውስጥ ከተዘረፈው ጥቂቱ ነበር። ከጥቂቱ በስተቀር የሁሉም ኩባንያዎች ዋና ጽህፈትቤቶች ማለት ይቻላል በመቀሌ ከተማ ሆኑ። የቦርድ አባላትና ሀላፊዎች የህውሀት ማእከላዊ ኮሚቴና ከፍተኛ አመራር አባላት ሆኑ።

 

ወያኔ ይህንን ኢኮኖሚውን በቁጥጥሩ ስር የማስገባት እንቅስቃሴ ሲያካሂድ፤ እንደሽፋን ያቀርቡት የነበረው ወሬ፤ ትግራይን መልሶ ለማቋቋም ወይም በጦርነቱ ለተጎዱ አካባቢዎች ቅድሚያ በመስጠት መልሶ ማቋቋም የሚል ነበር። በመሰረቱ በጦርነቱ የተጎዳው መላው   የኢትዮጵያ ህዝብና ሀገሪቱ እንጂ አንድ ክፍለ ሀገር ብቻ አልነበረም። ከሀገሪቱ በጀት ስልሳ ከመቶ የሚሆነው ለጦርነቱ ይውል ነበር። ያሁሉ ስንት ነገር ማልማት የሚችል ሀብት በነሱ ምክንያት ይባክን ነበር። እነሱ በሀገሪቱ ታሪካዊ ጠላቶች እየተረዱ ሲዋጉ፤ እኛ በጓዳ ማጀት ያለንን እያሟጠጥን እንታገል ነበር። በሁለቱም ወገን ያለቁት ተዋጊዎች  የሀገሪቱ ልጆች ናቸው።

 

ሁለት ወንድማማቾች አንደኛው እርጉም ይሆንና፤ የጋራ ቤታቸውን አፈርሳለሁ ሲል፤ ሌላኛው ወንድም የለም አታፈርስም። መሰብሰቢያችንን አትንድም። እያለ ሲታገል፡ እርጉሙ በጠላት እየተረዳ እየታገዘ ሲታገል ይኸኛውም ወገን ቤት እንዳይፈርስ የቻለውን ሁሉ ሲያደርግ፤ ጦርነቱ በእርጉማኑ አሸናፊነት ተጠናቀቀ።ቤቱም ፈረሰ።እርጉሙ ወገን ቤቱን በማፍረስ አላቆመም። ወንድሞቹን ሁሉ አግልሎ፤ እነሱን ከፋፍሎ እያባላ፤ እንደጀመረው ከባእዳን ጋር ብቻ እየተወዳጀና እየመከረ የራሱን የበላይነትና ጥቅም መገንባቱን ቀጠለ። 

 

እነዚህ ሰዎች ወታደሮም ናቸው። ነጋዴዎችም ናቸው። መንግስትም ናቸው። የሀገሪቱን ሀብትና ስልጣን ይዞ ለመዝለቅ ወታደራዊ እርምጃም ይጠቀማሉ። አስተዳደራዊ ስልጣንም ይጠቀማሉ። ሕግም ይፈጥራሉ ይጠቀማሉ። የመከላከያው፤ የደህንነቱ፤ የፖሊሱ ሀላፊዎች፤ ከየኩባንያዎቹ ከሚገኘው ትርፍ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ተካፋይ በመሆናቸው፤ የአርባ፤የሐምሳ ሚሊዮን ብር ፎቅ እያስገነቡ በማከራየት ላይ ናቸው። አንድ የወታደር አዛዥ በምን መልኩ ነው የሀምሳ ሚሊዮን ፎቅ ገንብቶ ባለሀብት ሊሆን የሚችለው? ያውም ሀያ አመት ብቻ ያገለገለ፤ በተራ ሽምቅ ውጊያ የሰለጠነ፤አግባብነት ያለው የሚሊታሪ ኮሌጅ ተምሮ ሳይሆን እንዲሁ ኮሎኔል ጀነራል የሚል ስም የተለጠፈለት የመሀይም ሽፍታ ጥርቅም። በስርአቱ ላይ የሚነሳ የስልጣን ጥያቄ በቀጥታ በነዚህ ሰዎች ጥቅም ላይ የሚመጣ ስለሆነ አጥብቀው ህዝቡን ሊወጉት ይችላሉ። ከሀያ አመት በፊት የረባ ጫማና ልብስ አንኳ ያልነበራቸው ዛሬ  ቢሊየነሮች ናቸው። ከየት አመጡ? ማንም የሚመልሰው አጭር መልስ ኢትዮጵያን ዘረፏት ነው። ህዝቡን ዘረፉት ነው። ከታች ያለው ሰፊ የህዝብ ልጅ፤ ወታደሩ መሳሪያውን በነሱ ላይ ካዞረ ነገሩን ሁሉ ሊያቀለው ይችላል። በነሱ መነዳቱ ከቀጠለ የህዝቡን ትግል ሊያከብደው ይችላል።

 

ኢኮኖሚውና ፖለቲካው እንግዲህ አሁን በጥቂት የትግራይ ታጋዮች የበላይነት ስር ወድቋል። ነባር ሀብታሞች አፈር ልሰው የተነሱ ታታሪ ኢትዮጵያውያን፤ ትግሬ ያልሆኑ ዜጎች ከጨዋታ ውጭ እየተደረጉ በሀያ አመት ውስጥ ከሰማይ ዱብ ያሉ ቢሊየነሮች እየተኳቸው ይገኛሉ። ከንግዲህ ጊዜውም ሀድራውም በቁጥር መቶም ይሁኑ ሁለት መቶ የወያኔ መሪዎች ይሆናል ማለት ነው።

 

በሚቀጥሉት ጥቂት አመታት ውስጥ የጉራጌ ባለሀብት አይኖርም።የአማራ የኦሮሞ የሌላውም ሁሉ ባለሀብት አይኖርም። በኢትዮጵያ ውስጥ በአፍሪካ ምናልባትም ብቸኛ የሆነ የድሀ አገር ሞኖፖሊ ካፒታሊዝም ይፈጠራል። እነዚያም ጥቂት ታጋይ የነበሩ ትግራይ ሰዎች ይሆናሉ። የቀረው ህዝብ የነሱ ሰራተኛና ጭሰኛ ይሆናል ማለት ነው።

 

በትግል ወቅት ከባዱን ስራ የሚሰሩት ጀግኖች ይሞታሉ። ፈሪዎቹ፤ አፈጮሌዎቹ፤ ሸፍጠኞቹና አስመሳዮቹ፤ የዋሆቹንና ጀግኖቹን እያስቀደሙ፤ እያገፋፈጡ አነሱ ይድናሉ። ሗላ ላይ የመስዋእትነቱ ፍሬ ቀማሽም ይሆናሉ። የድሉ ባለቤትም ይሆናሉ።

 

መለስ ዜናዊ የአድዋ ከተማን ባንክ እንዲዘርፍ ድርጅቱ ተልኮ ሰቶት፤ ጦር እየመራ አድዋ ከተማ በምሽት ከገባ በሗላ፡ የመጀመሪያዋ መትረየስ ስትተኮስ ሰራዊቱን ጥሎ የጠፋ የሸሸ ነበር። ቁጥራቸው በቀላል ለማይገመት ታጋዮች ማለቅ ምክንያት በመሆኑ፤ ታጋዮቹ መገደል እንዳለበት ወስነው፤ በእንዴት ያለ ሻጥር በወቅቱ ሳይገዳል እንደቀረ፤ ዛሬ በስደት ያሉ የትግል አጋሮቹ ያስረዳሉ። የነዚያ ጀግኖች ደም ያስገኘው ጥቅም ባለቤት ግን እሱና የፖለቲካውን ቁማር ይጫወቱ የነበሩ ባልደረቦቹ ሆነ።                                        

 

በጀግንነት ደማቸውን አፍሰው እነዚህን ጥቂት የቀን ጅቦች ለድል ያበቋቸው የትግራይ አርሶ አደር ልጆች፤ ለኢትዮጵያ ሰላምና ዲሞክራሲ ታመጣላችሁ ተብለው ተዋጉ እንጂ ጥቂቱን የሕውሀት መሪዎች በቢሊየን ብር ለማንበሽበሽና ለማደለብ አልነበረም በረሀ የገቡት።

 

አራት ልጅ፤ አምስት ልጅ፤ እያፈኑና በፕሮፓጋንዳ እያታለሉ በጦርነቱ ያስፈጁባት ድሀ የትግራይ እናት፤ ድሀ የትግራይ አባት፤ ድሀ የትግራይ አርሶ አደር፤ ምናልባትም ሁሉም በልጆቻቸው ሀዘን ተጠብሰው አልቀዋል። ሞተዋል። ቢኖሩም እንደማንኛውም የኢትዮጵያ ህዝብ በድህነት ተጨብጠው የመከራ ህይወት በመግፋት ላይ ናቸው። አንዳቸውም ግን በልጆቻቸው ደም በተገኘው ድል ተዘርፎ የተቋቋመው ኩባንያ ሼር ሆልደር አይደሉም። ምናልባት በያመቱ ማዳበሪያ ካልወሰዳችሁ እየተባሉ በደከመ ጉልበት ያዘመሯትን ያመት ቀለብ የተበደራችሁትን ማዳበሪያ ክፈሉ አየተባሉ ያችኑ ከድብኝት እያራገፉ እየሸጡ ሚሊየነሮቹን በማደለብ ላይ ናቸው። ልጆቻቸውን የገበሩት አልበቃ ብሎ።

 

ከማንኛውም የኢትዮጵያ ህዝብ የበለጠ የመከራ ገፈት እየቀመሰ ያለውን የትግራይ ህዝብ፤ የትግራይ አርሶ አደር፤ ከነዚህ ማፊያ ሰዎች ጋር እንዳታገናኙት። እነዚህ ማጅራት መችዎች የትግራይ ህዝብ ጀርባ ላይ እንደ መዥገር ተጣብቀው፤ እየዋሹትና እያታለሉትም እያስገደዱትም ለዚህ እንዳበቃቸው፤ አሁንም ለሚነሳባቸው ሁሉ ያንን መከረኛ ደራሽ የሌለው ህዝብ እያገፋፈጡ፤ የሌብነት እድሜያቸውን ማስረዘም ስለሚፈልጉ፤ የኢትዮጵያ ህዝብ መጀመሪያ የትግራይን ሀዝብ ነው ማዳን ያለበት። የነጻነቱ ትግል መጀመር ያለበት የትግራይን ህዝብ ነጻ በማውጣት ነው።

 

በዓጼ ሀይለስላሴ ዘመን ጉልተኞችና የመሬት ባላባቶች አርሶ አደሩ ለሚያርሳት መሬት ዋጋ በየአመቱ ያዘመረውን ወቅት እየጠበቁ የጎተራ የድብኝቱን እያሟጠጡ ብግር ብለው ይወስዱበት ነበር። ያለውን የቁም ከብት እየሸጠ እንዲከፍላቸው ያስገድዱት ነበር።ይህ በዛሬዪቱ ኢትዮጵያ ከፊውዳሉ ዘመን በከፋ መልኩ እየተካሄደ ያለ ግፍ ነው። የኢትጵያ አርሶ አደር የጥቂት ወያኔ ድርጅቶች የሀብት ምንጭ እየተደረገ ያለበት አሰራር ተፈጥሯል።

 

የህውሀት ኩባንያዎች ከውጭ የሚያስገቧቸውን ሸቀጦች ሸጠው ማትረፍ እንዳለባቸው ስልሚያምኑ፤ በግድ ህዝቡ ላይ ማራገፍና መገላገል አለባቸው። ማዳበሪያን ብንመለከት የሚታረሰው አካባቢ የቱንም ያህል ለም ቢሆን፤ የመሬቱ በኬሚካል ላይ ጥገኛ መሆን ወይም የገበሬው ገንዘቡን መቆጠብ የነሱ ጉዳይ አይደለም። ገበሬ ፈቀደም አልፈቀደ ማዳበሪያው ከውጭ የገባው እስከሚአልቅ ይታደላል።የአዝመራ ወቅት ሲደርስ ምን አዘመርክ? ስንት ቤተሰብ ትመግባለህ? አይደለም ጥያቄቄው። “ስንት ነው ያለብህ እዳ፤ በዚህ ጊዜ ውስጥ ገቢ አንድታደርግ” ነው የሚባለው።

 

አሁን ባገራችን ያለው የሀብት ክምችት ሚዛን በንጉሱ ዘመን ከነበረው ሁኔታ ጋር ይመሳለላል። በዚያን ዘመን መሬትና በርካታ የንግድ ኩባንያዎች በመኳንንቱና በመሳፍንቱ እጅ የተካማቹ ነበሩ። መሬትን ብንወስድ በንጉሱ ቤተሰቦችና መሳፍንት መኳንንት እንዲሁም አንዳንድ ታማኝ ከፍተኛ የጦር አለቆች ንብረትና ሀብት ነበር። ያኔ አርሶ አደሩ የኔ የሚለው መሬት ነበረው ወይ? የለውም። አሁን የኢትዮጵያ አርሶ አደር የኔ የሚለው መሬት አለው ወይ? የለውም ።ዛሬ መሬቱን የተቆጣጠሩት የትግራይ ታጋዮች ቅድመ አብዮት መሬት ላራሹ ብለው አልጮሁም ነበር ወይ? ጮኸዋል። ታዲያ ዛሬ መሬቱን ተቆጣጥረዋል፤ ለምን መሬትን ላራሹ አላደረጉም? ለምን አርሶ አዱን ሰሰቱበት? ያ የሞተው መሪያቸው ይል እንደነበረው የአማራው ባለሀብት እንደገና መሬቱን አንዳይቆጣጠረው ሰግተው ነው? መሬት የመንግስት ነው። መንግስት ህውሀት ነው። እና ብለው የመንግስትና የብሄር ብሔረሰቦች ነው።አፍጦ አግጦ የምናየው እውነታ ግን መሬት የህውሀትና የውጭ የንግድ ሽርካዎቻቸው ነው። የኢትየጵያ አርሶአደር ዘለአለማዊ ጭሰኛ ነው።                                     

 

የኢትዮጵያ አርሶ አደር ተደራጅቶ አምጾ መሬቱንና መብቱን ነጻነቱን ከነዚህ የቀን ጅቦች ካልነጠቀ፤ ጥቂት የህውሀት አመራር ባለሀብቶችን እያደለበ እርሱ እስከዘላለም በባርነት መኖሩ አይቀሬ ነው።                                                                                     

 

አቶ አስገደ ገብረስላሴ ወልደሚካኤል በትግራይ ውስጥ እየተዘዋወሩ የአርሶ አደሩን ሰቆቃ ሲያጠኑ፤ በኢትዮሚዲያ ድረገጽ ላይ ያወጡት ጽሁፍ በዋቢነት ሲጠቀስ፤ አርሶ አደሮች በብዛት የጋማና የቀንድ ከብቶቻቸውን ወደ ገበያ ሲነዱ አይተው፤ ገበያተኛውን አነጋግረው፤ ያገኙት መልስ “….እኛ ባሁኑ ጊዜ በአንድ በኩል የደደቢት ብድርና ቁጠባ፤ በሌላ በኩል የፓኬጅ፤ በተጨማሪ የማዳበሪያ ግዢ ብድር ክፈሉ፤ ካለበለዚያ ንብረታችሁና ሰብላችሁ ይወረሳል ስለተባለ ተደናገጥን። በአሁኑ ጊዜ የትግራይ አርሶ አደርና አነስተኛ ነጋዴ፤ ከአምስት አመት በላይ ውዝፍ እዳ አለበት…..” ብለው አርሶ አደሮቹ ነግረዋቸዋል።

 

አቶ አስገደ በዚያው ጽሁፋቸው ላይ ወረድ ብለው እያንዳንዳቸው ሀያ አምስት አባወራ ያሉባቸውን አራት መንደሮችን አጥንተው የታዘቡትን ሲነግሩን “…የሚገርመው ነገር በሶስቱ ጎጦች ያሉ ገበሬዎች መቶ በመቶ እዳ አለባቸው። በአንዱ ጎጥ ሶስት ሰዎች ብቻ እዳ የሌለባቸው አገኘሁ… የህውሀት መሪዎች ግን 4.3 ሚሊየን የሆነውን የትግራይ ህዝብ አንጡራ ሀብት በእጃቸው ለማስገባት ብለው ያቋቋሙት የደደቢት ፍትሀዊ ብድርና ቁጠባ፤ ፍትሀዊ ሳይሆን የትግራይን ህዝብ ግብኣተ መሬት ያስገባ እና ህዝብ፤ አባትና ልጅ፤ ባልና ሚስት የበታተነ፡ የህውሀት የንግድ ድርጅት ነው…” በማለት ነበር ቁኝ ቁልጭ አድርገው የትግራይን ህዝብ ሰቆቃ ያቀረቡት።…አቶ አስገደ።

 

ውድ አንባቢያን ከዚህ በታች እንደ አባሪ አድርጌ የማቀርበው ሰነድ የግንቦተ ሰባት ድረገጽ ይዞት የወጣ ሲሆን በዛሬዪቱ ኢትዮጵያ ያሉትን ባለሀብቶች ያመለክታል። በዚያውም ነገሩ ሁሉ ወዴት እንደሚያመራ ግንዛቤ ያስጨብጣል። ልብ ብላችሁ ተመልከቱት።

 

Full List of TPLF Companies Under EFFORT

Companies with investment capital of < 20,000,000 Million Ethiopian Birr

Company Name

Year Est.(EC)

Capital

HQ

Board Chairman

Selam Transport

1995

10,000000 Birr

Mekele

Arkebe Ekubay

Segel Construction

1995

10,000,000 Birr

Mekele

Araya Zerihun

Mega Net Corp

1995

10,000,000 Birr

Mekele

Alemseged Gebreamlak

Hitech Park Axion Association

1995

10,000,000 Birr

Mekele

Shimelis Kinde

Fana Democracy plc

1995

6,000,000 Birr

Mekele

Negash Sahle

Express Transit

1995

10,000,000 Birr

Mekele

G/selassie Gidey

Ethio Rental Axion Association

1995

10,000,000 Birr

Mekele

Atkilit Kiros

Dilate Brewery

1995

15,000,000 Birr

Mekele

Kahsay TewoldeTedla

Dessalegn Caterinary

1995

15,000,000 Birr

Mekele

Dr, Maru Erdaw

Addis Consultancy House

1995

10,000,000 Birr

Mekele

Sibhat Nega

Birhane Building Construction

1995

10,000,000 Birr

Mekele

Bereket Mazengiya

Total Capital

 

116, 000,000 birr

 

 

Companies with investment capital between 20-49 Million Ethiopian Birr

Company Name

Year Est (EC)

Capital

HQ

Board Chairman

Sheba Tannery Factory Axion Assoc.

1995

40,000,000 Birr

Wukro

Abadi Zemu

Meskerem Investment

1995

40,000,000 Birr

Axum

Tewodros Ayes Tesfaye

Africa Insurance Axion Association

1995

30,000,000 Birr

A.Ababa

Yohannes Ekubay

Global Auto Sparepart

1995

26,000,000 Birr

A.Ababa

Teklebirhan Habtu

Experience Ethiopia Travel

1995

26,000,000 Birr

Mekele

Tony Hiki

Addis Engineering Consultancy

1995

25,000,000 Birr

A.Ababa

Arkebe Ekubay

Hiwot Agriculture Mechanization

1995

25,000,000 Birr

Mekele

Yohannes Kidane

Berhe Chemical Axion

1995

25,000,000 Birr

Mekele

Abadi Zemu

Rahwa Yebegina Fiyel Export

1995

25,000,000 Birr

Mekele

Yassin Abdurahman

Star Pharmaceuticals

1995

25,000,000 Birr

Mekele

Arkebe Ekubay

Tesfa Livestock

1995

20,000,000 Birr

Mekele

Yohannes Kidane

Total Capital

 

 307,000,000 Birr

 

 

 

Companies with a paid-up capital of >50.000.000  Million Ethiopian Birr 

Company Name

Year Est.(EC)

Capital

HQ

Board Chairman

Almedan Garment Factory

1995

660,000,000 Birr

Mekele

Abadi Zemu

Mesfin Industrial Company

1995

500,000,000 Birr

Mekele

Arkebe Ekubay

Mesob Cement Factory

1995

240,000,000 Birr

Mekele

Abadi Zemu

Almeda Textile Factory

1995

180,000,000 Birr

Mekele

Abadi Zemu

Sur Construction

1995

150,000,000 Birr

A.Ababa

Arkebe Ekubay

Trans Ethiopia

1995

100,000,000 Birr

Mekele

Shimelis Kinde

Dedebit Saving & Loan

1995

  60,000,000 Birr

Mekele

Atkilit Kiros

Ezana Mining Development

1995

  55,000,000 Birr

A.Ababa

Tewodros H. Berhe

Addis Pharmaceuticals Production

1995

  53,000,000 Birr

A.Ababa

Abadi Zemu

Tana Trading House Axion Association

1995

  50,000,000 Birr

A.Ababa

Sibhat Nega

Total Capital

 

 1,868,000,000 Birr

 

 

Companies that did not make their paid-up capital public

Ambassel Commerce

Dinsho Share Company

Tigrai Tagai Association

Brook Chemical Share Company

Dashen Beer Factory

Express Ethio Travel Service

Tigrai Development PLC

Computer Networking Technology

Amhara Meleso MaquaQuam

Berhan Building Construction

Star Pharmaceutical Importers

National Electromechanical

Saba Emnebered

Guna Trade Services

Biftu Dinsho

Oromia Credit Bank

Adwa Flour Factory

Wendo Trading

Shala Advertisement

National Geo-Textile

Trans Ethiopia

Tikal Agri Tigrai

Wegagen Bank

Alage Forest Products

Sebhat Nega PLC

Addis Transport

Walta Industry

Martha poultry

Dima Honey Processinf plant

Zeleke Agricultural Mechanization PLC

Tikur Abbay Transport

Beruk Tesfa Plastic Factory

Aberdele Animal Export Company

Maichew Particle Board

 

 

These 66 companies are owned and managed by ethnic Tigreans
*Some Board Chairmen might have moved within the parastatals
*The amount shown on the tables above are initial start up capitals. The total networth of the parastatals has quadrupled                                                                                                                                                                         

This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. 

 

አዲስ ቪዲዮ

ይከተሉን!

ስለእኛ

መጻሕፍት

ቪዲዮ

ኪነ-ጥበብ

ዜና እና ፖለቲካ