ዶ/ር ቴዎድሮስ አድኃኖም በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ራሳቸውን አገለሉ
የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴዎድሮስ አድኃኖም
ከአንድ በቫይረሱ ከተያዘ ሰው ጋር ተገናኝተው ነበር
ኢዛ (ሰኞ ጥቅምት ፳፪ ቀን ፳፻፲፫ ዓ.ም. November 2, 2020)፦ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴዎድሮስ አድኃኖም በኮሮና ቫይረስ ከተያዘ አንድ ግለሰብ ጋር መገናኘታቸውን በማስታወቅ፤ ራሳቸውን ማግለላቸውን ዛሬ ሰኞ ጥቅምት 22 ቀን 2013 ዓ.ም. በትዊተር ገጻቸው አሳወቁ።
በቅርብ ጊዜ ውስጥ ያገኙት ይህ ግለሰብ የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘበት በመረጋገጡ፤ ራሳቸውን በማግለል ሥራቸውን ከቤት ኾነው ለመሥራት መወሰናቸውንም ገልጸዋል።
ጤንነታቸውን በተመለከተም በአሁኑ ወቅት ምንም ዐይነት የቫይረሱ ምልክት የማይታይባቸው ስለመኾኑ በዚሁ የትዊተር ገጻቸው ላይ አመልክተዋል። (ኢዛ)



